Saturday, October 12, 2013

14 ዓመታት ተፈርዶበት እስር ቤት የሚገኘው ውብሸት ታዬ የሲኤንኤንን ሽልማት አሸነፈ


(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው የሚዲያ ተቋም ሲኤንኤን (Cable News Network) በየዓመቱ የሚያዘጋጀው የመልቲ ቾይዝ የአፍሪካ ሽልማት ሥነ-ሥርዓት ዛሬ ተካሄደ። በዚህ የሽልማት ስነስርዓት ላይ በ እስር ቤት የሚገኘው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ አሸናፊ መሆኑን ዘ-ሐበሻ ሽልማቱን በትዊተር በመከታተል ካገኘችው መረጃ ለማወቅ ተችሏል።

በተለያዩ ዘርፎች ሲኤን ኤን የአፍሪካ ጋዜጠኞችን በየዓመቱ የሚሸልም ሲሆን ከዚህ ዓመት ተሸላሚዎች መካከል ኢትዮጵያዊው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ሽልማቱን ያገኘው Free Press Africa Award በሚለው ዘርፍ ነው።
በእስር ቤት ከ2 ዓመት ከ4 ወር በላይ የሆነው ጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ ይሰራበት በነበረው አውራምባ ታይምስ ጋዜጣ ላይ ሽብርተኝነትን የሚያበረታታ ጽሁፍ ጽፈሃል በሚል 14 ዓመታት ተፈርዶበት እስር ላይ ይገኛል። የዛሬውን የሲኤን ኤን ሽልማት እርሱ እስር ላይ በመሆኑ ባለቤቱ መምህርት ብርሀን ተስፋዬ እና ልጁ ፍትህ ውብሸት በደቡብ አፍሪካ ኬፕ ታውን ኢንተርናሽናል ኮንቬንሽን ሴንተር በመገኘት መቀበላቸውን ዘ-ሐበሻ በትዊተር በመከታተል ያገኘችው መረጃ ያመለክታል።
ለጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ መታሰር ለሕወሓት/ኢሕአዴግ ደህንነቶች ጥቆማውን በመስጠት ደረጃ ማንን ትጠረጥራላችሁ? እኛ እያጣራነው ያለነው ጉዳይ አለ፤ እናንተ ግን አስተያየታችሁን በአስተያየት መስጫው ያስቀምጡ።

No comments:

Post a Comment