Monday, September 30, 2013

Ethiopia: Muslims' struggle for rights continues (analysis)

Think Africa Press, by Joris Leverink* / Monday, 30 September 2013



Muslims in Ethiopia have been protesting against government interference in religious affairs for more than twenty months. But ever since the violent crackdown by Ethiopian security forces on peaceful protestors during the Eid al-Fitr celebrations in Arsi last month, the Muslim community has been wary of organising new rallies. Whereas some observers believe that the movement has lost its momentum, activists engaged in the protests vow to continue their peaceful resistance until their demands are met.

The protestors identify themselves as a civil movement and have three clear demands: for the government to stop meddling with religious affairs; the right to elect the members of the High Islamic Council known as the Majlis; and for their leaders, who have been jailed for over a year under "trumped-up" charges, to be released.
During the past a year and a half of demonstrations, several protestors have been killed by the security forces, and dozens, if not hundreds, have been arrested or taken into custody. The Ethiopian Government has denied allegations of police brutality and called accusations of human rights abuses that were made by Amnesty International, "one-sided and largely inaccurate, based on hearsay, political calculation or, all-too-often, downright invention."

“ፕሬዚዳንት እንድሆን ብጠየቅ በቅድሚያ ምን ያህል ላገለግል እችላለሁ እላለሁ – ወ/ሮ ሰሎሜ ታደሰ

Selome Tadesse

የቀድሞዋ የመንግስት ቃል አቀባይ ወ/ሮ ሰሎሜ ታደሰ ሃገር ቤት ከሚታተመው ሎሚ መጽሔት ጋር ቃለ ምልልስ አድርጋለች። የዘ-ሐበሻ አንባቢዎች ግንዛቤ ይረዳቸው ዘንድ ቃለ ምልልሱን እንደወረደ አስተናገድነው…

ሁሉ ነገር ራዕይ ሆኖ ይቀጥላል እንዲባል አልፈልግም
በሥልጣን የሚመጣ ክብር ደግሞ ከሥልጣን ጋር አብሮ ይቀራል

ሎሚ፡- አምባሣደር ዮዲት እምሩ በሕይወትሽ ከፍተኛ መነቃቃት እንደፈጠሩብሽ ይሰማል፤ እንዴትና ለምን?
ወ/ሮ ሰሎሜ፡- እሳቸው ከፈጠሩብኝ መነሣሣትና መነሳሳት ይልቅ አባቴ እሳቸውን ምሣሌ በማድረግ ውስጤ የፈጠረው መነሣሣት ነው የሚበልጠው፡፡ ልጅ እያለሁ እሣቸው አምባሣደር ነበሩና በቴሌቪዥን በተደጋጋሚ ይታዩ ነበር፡፡ የዛን ጊዜ እኔ አራተኛ ክፍል ነበርኩ፡፡ ሁልጊዜም በቴሌቪዥን ሲመጡ አባቴ ይጠራኝና “…በቃ አንቺ ስታድጊ እሣቸው ስራ የላቸውም” ይለኝ ነበር፡፡ የእሱ አባባል ስታድጊ ስራቸውን ትወስጅባቺዋለሽ ዓይነት ነበር፡፡ የመጀመሪያዋ ሴት እንደዚህ ታላቅ የሚባል ስራ ይዘው በቴሌቪዥን መጥተው ያየኋቸው እሳቸው ናቸው፡፡ እሣቸው ላይ ይበልጥ ትኩረት እንድሰጥና እንድነቃቃ ያደረገው ደግሞ አባቴ ነው፡፡
ሎሚ፡- ያኔ ልጅ እያለሽ አምባሣደር ዮዲት የፈጠሩብሽ አይነት ስሜት አሁን በሌሎች ትናንሽ ሴት ልጆች ላይ መፍጠር ችያለሁ ብለሽ ታስቢያለሽ?
ወ/ሮ ሰሎሜ፡- እንደዚያ ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ፡፡ ሁሌም የምለው ነገር ነው፤ ሁሉም ሰው እዚህች ምድር የመጣው ለምክንያት ነው በሚለው አምናለሁ፡፡ ምክንያት ደግሞ የሆነ ተፅእኖ የሚያሣድር ማለት ነው፡፡ ያ ተፅእኖ ደግሞ ጥሩ ነገር ለመስራትና ለማነሳሳት አርአያ ለመሆን ቢሆን ደስ ይለኛል፡፡ ወጣት ሴቶች እሷን አይቼ ነው ይህን የሆንኩት ቢሉ ደስ ይለኛል፡፡ ከዚህ ሌላ ደግሞ ከአንዳንድ ሴቶች ጋር ስንገናኝ… “አንቺ በኢትዮ ኤርትራ ጦርነት ወቅት ቃል አቀባይ በነበርሽበት ወቅት የምትናገሪውን እሰማ ነበር፤… በዛ ምክንያት እንዲሕ አድርጌ…” ሲሉኝ ደስ ይለኛል፡፡ በርግጥ እነሱ ይህንን ይላሉ፣ ወደፊት እንዲሕ እባላለሁ… ብዬ ባልንቀሳቀስም… መንገዱ ግን ያንን ፈጥሮ ከሄደ በጣም ደስ ይላል፡፡ እናም እፈጥራለሁ የሚል እምነት አለኝ፡፡
ሎሚ፡- የሕይወት ፍልስፍናሽ ምንድን ነው?
ወ/ሮ ሰሎሜ፡- ከባድ ጥያቄ ነው ብዙ ጊዜ የሚከብደኝ ጥያቄ የሕይወት ፍልስፍናሽ ምንድነው የሚለው ነው፡፡ በአንድ ወቅት የነበረ ፍልስፍና በሌላ ወቅት ሊቀየር አይችልም ወይ ብዬ አስባለሁ፡፡ በተለይ የራሴን ወደኋላ መለስ ብዬ ሳስታውስ… ከልጅነቴ ጀምሮ የያዝኩት ፍልስፍና ነው ለማለት ይከብደኛል፡፡ ምክንያቱም ፍልስፍናን ራሱን ለመተግበር አቅም ይጠይቃል፡፡ ግን አሁን ዛሬ በአጭሩ ምንድነው ፍልስፍናሽ ብትለኝ በዚህች ምድር ላይ ዱካ የጣለ፣ ኮቴ የነበረው ሰው፣ ኮቴው የተሰማ ሰው ሆኖ ማለፍ፡፡ …read more
Via: Zehabesha

ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ይህንን የማፊያ ቡድን በማፍረስ ታሪክ ይስሩ! በግርማ ሠይፉ ማሩ

ግርማ ሠይፉ ማሩ
በ2005 ዓ.ም የምክር ቤት ዘመን መጨረሻ ላይ የደህንነት መስሪያ ቤቱን በሚኒስትር ደረጃ ለማዋቀር የሚረዳ አንድ አዋጅ ለምክር ቤት ቀርቦ ፀድቆዋል፡፡ ይህ አዋጅ ሲፀድቅ ከነቅሬታዬ ያለኝ ድጋፍ መስጠቴ ይታወቃል፣ ለዚህ አዋጅ ድጋፍ መስጠት የፈለኩት ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ ከበረሃ ይዘውት የመጡት ልዩ ልዩ አፋኝ ቡድን ስለማይኖራቸው እንዲሁም ቀደም ሲል የነበሩትን አፋኝ ቡድንች ወደ አንድ መዋቅር በማጠቃለል ተጠሪነቱ ከተለያዩ መዋቅሮችና ግለሰቦች ወደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ (ወደ ተገቢው ማለት ነው) ቁጥጥር በማስገባት ለዜጎች ስጋት ሳይሆን ለዜጎች እና ለሀገር ደህንነት የሚስራ ተቋም ይሆናል በሚል ተስፋ ነው፡፡ ይህ ተስፋዬም ዝም ብሎ ሳይሆን በአዋጁ አንቀፅ 3 “ይህ አዋጅ በመላው ሀገሪቱ ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ በፌዴራልም ሆነ በክልል መንግስታት ደረጃ ሌላ የመረጃና ደህንነት ተቋም  ማቋቋም አይቻልም” የሚል ድንጋጌ በመያዙ ነው፡፡ በመስከረም 19 እሁድ ዕለት አንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በጠራው ሰላማዊ ሰልፍ “በሰላም” ከተጠናቀቀ በኋላ እጅግ አሰገራሚ የሆነ ተግባር አጋጥሞናል፡፡ ተስፋዬንም ስለአጨለመብኝ ይህን ጉዳይ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትሩ እንዲያውቁትና የብሔራዊ የመረጃና ደህንነት አገልግሎቱ ኃላፊውን ጠርተው ማብራሪያ እንዲጠይቁ መነሻ ለመስጠት ነው፡፡
የፓርቲያችን ወጣቶች በሰልፉ ላይ ወጣቶችን፣ ሙስሊሙን፤ ክርስቲያኑን፣ ሴቶችን እንዲሁም በግፍ የታሰሩትን ዜጎች በተመሳሌነት ለማሳየት እጃቸውን እና እግራቸውን በሰንሰለት አስረው ከፊት ሆነው ሰልፍ ላይ ሲታዩ ነበር፡፡ ማንነታቸው ያልታወቀ ሲቪል የለበሱ ሰዎች ከነዚህ ወጣቶች አንዱን ጎትተው ከታክሲ በማውረድ ወደ መኪና ውስጥ ለመጫና ሲሉ በአካባቢው የነበሩ የአንድነት ወጣቶች ደርሰው መውሰድ አትችሉም በሚል ግርግር ሲፈጠር በቦታው ደረስኩ፡፡ በቦታው ደርሼ ይህን የሚፈፅሙትን ሰዎች መታወቂያ እንዲያሳዩኝ ሰጠይቅ ፈቃደኛ ባለመሆናቸው በአካባቢው የነበሩትን ፖሊሶች (ባለ ኮከብ ማዕረግ ያለቸው ጭምር) አስጠርቼ መታወቂያ እንዲያሰዩን እንዲያደርጉ ቢሞከርም እነዚህን ጉልበተኞች መታወቂያ ሊጠይቅ የሚችል ሞራል ያለው ፖሊስ አጣን፤ ህዝብ በተሰበሰበበት ፖሊሶችን እንዴት እንደሚያደርጓቸው ማየት በእውነት በምን ሁኔታ ላይ እንዳለን የሚያስገነዝብ ነው፡፡ በዚህ አጋጣሚ ከፖሊሶቹ አንዱ ጠርቶኝ እነዚህ እኮ ከእኛ አቅም በላይ ናቸው ሲለኝ በቅርቡ በኢሳት ቴሌቪዥን ቀርቦ ምስክርነት የሰጠው የፖሊስ መኮንን ትዝ ብሎኝ የመንግስታችን ባሕሪ አሁንም ለውጥ እያሳየ ያለመሆኑ እና ፊት ለፊት ከምናያቸው ተቋሞች ጀርባ ሌላ ስልጣን እንዳለ ፍንትው ብሎ ታየኝ፡፡ የሚገርመው በዚያው ዕለት እኔን እያወቁኝ መኪናዬን በግዳጅ አሰቁመው መንጃ ፈቃድ፣ በሚያስገርም ሁኔታ የመኪና ባለቤትነት ደብተር፣ ሰለቦሎ ዕድሳት የማያገባቸውን ሁሉ እየጠየቁ ታዘን ነው በሚል ከገዢው ፓርቲ ጋር በመተባበር ስልፉ እንዳይሳካ  ሲሰሩ የነበሩ ፖሊሶች በሰዓታት ልዩነት መታዊቂያ ያለመጠየቅ ስልጣን ያላቸው ልዩ ዜጎች እንዳሉ አስገንዝበውናል፡፡ ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እነዚህን ሰዎች ማንነት ማወቅ ከፈለጉ ፎቶና ቪዲዮ በእጃችን እንደሚገኝ ላረጋግጥሎት እችላለሁ፡፡ ሲቪል የለበሱ አፋኞችን ሳይሆን ዩኒፎርም የለበሱ ፖሊሶችንም ቢሆን መታወቂያ መጠየቅና ከወሮበላ ዱርዬ እራሳችን መጠበቅ መብታቸን እንደሆነ ግን ይታወቃል፡፡
በነገራችን ላይ ሰልፉ ከተጠናቀቀ በኋላ እነዚሁ ማፊያ ቡድኖች ፎቶ ይዘው ወጣቶችን በየመንገዱ እያስቆሙ እነዚህን ወጣቶች ማደን እንደያዙ ያረጋገጥን ሲሆን በዕለቱ ለደህንነታቸው ሲባል በአጀብ ወደ ቤታቸው ለማድረስ የቻልን ቢሆንም አሁንም እነዚህ ወጣቶች በምንም ዓይነት ሁኔታ ጉዳት ቢደርስባቸው ሌላ ምክንያት የሌለ እና ይህ የተደራጀ የማፊያ ቡድን የሚሰራው ስራ መሆኑን ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትር እንዲያውቁት እፈልጋለሁ፡፡ በማፊያዎቹ በመታደን ላይ ያሉት ወጣቶች ስንታየሁ ቸኮል፣ ዳንኤል ፈይሣ፣ ፋናዬ ወ/ጊዮርጊስ፣ ኤፍሬም ሰለሞን እንዲሁም አበበ ቁምላቸሁ የሚባሉ መሆናቸው እርሶም የዓለም ህብረተሰብም እንዲያውቀት መግለፅ ተገቢ መስሎ ታይቶኛል፡፡ በአደባባዩ ላይ ሲያሳዩ የነበረውም ምስል ይህንን ይመስላል፡፡ ወንጀላቸው ይህ ከሆነ ማለት ነው፡፡

Hiber Radio: “ኢትዮጵያ የሽማግሌ ያለህ እያለች ነው” – ዶ/ር አክሎግ ቢራራ

ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ

የህብር ሬዲዮ ዕሁድ መስከረም 19 ቀን 2006 ፕሮግራም
> ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ ለህብር ከሰጡት ቃለ ምልልስ የተወሰደ
>
አቶ ተካ ከለለ በአትላንታ የቲኬ ሾው አዘጋጅ
ጋዜጠኛ ሃብታሙ አሰፋ
> ስለ መስቀል በዓል ከተጠናቀረው ዘገባ
አልሸባብ እውን ለኢትዮጵያ ስጋት አይደለም(ልዩ ዘገባ)
> ዶ/ር አክሎግ ቢራራ
(ሌሎችም ቃለ መጠይቆች አሉን)
ዜናዎቻችን
ግብጻውያን በኢትዮጵያ ላይ ዛሬም ማጉረምረም ቀጥለዋል
ስዊድናዊ ዜግነት ያላት ኢትዮጵያዊቷ አትሌት አበባ የዘረኝነት ሰለባ መሆኑዋን ገለጸች
የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት ሰልፍ በፖሊስ ታግቶም ከ80 ሺህ ሰው በላይ ወጥቶ ተቃውሞውን አሰማ
ዶ/ር ነጋሶ ኢህአዴግ ተገዶ መስቀል አደባባይን ጨምሮ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ እንቅስቃሴው ይቀጥላል አሉ
የመን በኤርትራ ተያዙ ያለቻቸውን ዜጎቿን ለማስለቀቅ መዘጋጀቷን ገለጸች
የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሐይል በኖርዌይ የተሳካ የገቢ ማሰባሰብ አካሄደ
የአገዛዙ ደጋፊዎች ስብሰባውን በአሸባሪነት ከሰው ለማደናቀፍ ያልተሳካ ሙከራ አደረጉ
ሌሎችም ዜናዎች አሉን
Via: Zehabesha

Sunday, September 29, 2013

“መስቀል የሚያቃጥል (አይደለም)”

ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ሲኖዶሡ ውሣኔ ይሰጣል - አቡነ እስጢፋኖስ

abune estifanos

በአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ እስኪያስተላልፍ ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ የአዲስ አበባና የጅማ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አሣሠቡ፡፡ “መስቀል ከሠማይ ወርዷል አልወረደም? ትክክለኛ ነው አይደለም?” የሚለውን ለመመለስ የግድ ቅዱስ ሲኖዶሡ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው፤ ይህን ለማድረግም ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ቋሚ አባላት እንዳሣወቁ ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ እንደተባለው ከሠማይ የወረደ አለመሆኑ ከተረጋገጠም የቤተክርስቲያኒቱ ሃላፊዎች ይጠየቁበታል ብለዋል-ብፁዕነታቸው፡፡
መስቀሉ ከሠማይ ወረደ በተባለ በ4ኛው ቀን ነሐሴ 27 ቀን 2005 ከሠአት በኋላ ወደ ስፍራው በማቅናት ተገቢውን የፀሎት ስርአት ከካህናቱና ከቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ጋር ካደረሡ በኋላ መስቀሉን ከወደቀበት መሬት አንስተው ወደ ቤተመቅደሡ እንዲገባ ማድረጋቸውን የገለፁት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፤ መስቀሉ ከሠማይ ስለመውረዱ በአይናችን አይተናል ካሉት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እንደማንኛውም ሠው መስማታቸውን ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
መስቀሉን ከወደቀበት መሬት ያነሱት ብፁዕነታቸው፤ “መስቀሉ ያቃጥላል፤ ብርሃናማ ነፀብራቅ አለው” የሚባለውን አለማስተዋላቸውን ጠቁመው፤ “መስቀል የሚያቃጥል ሣይሆን የድህነት ሃይል ነው ያለው፣ የሚያቃጥል ቢሆን ኖሮ ከመሬት ላይ ማንሣት ባልተቻለ ነበር” ብለዋል፡፡ ወረደ የተባለውን መስቀል ለመመልከት ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ምዕመናን ለምን እንዳይመለከቱት ተከለከለ የሚል ጥያቄ ያነሣንላቸው ብፁዕነታቸው፤ ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶሡ ተጣርቶ ውሣኔ እስኪያገኝ ድረስ ህዝበ ክርስቲያኑ ጉዳዩን በጥሞና እንዲያጤነው በማሠብ ነው” ብለዋል፡፡ (ምንጭ: አዲስ አድማስ)

ስለህወሓት ፀረ-ኢትዮጵያ አካሄድ የተሸፈኑ ምስጢሮች

ስለህወሓት ፀረ-ኢትዮጵያ አካሄድ የተሸፈኑ ምስጢሮች

ገሰሰው አየለ፣ አግአዚ ገሰሰ፣ ሙሴ መሃሪ ተክሌ፣ አጽብሃ ዳኛው እና ዶ/ር አታክልት ቀጸላ Gessesew Ayele, Agazi Gessese, Musse Mahri Tekle, Atsbeha Dagnachew and Dr. Atakilt Ketswela
የህወሓትን ፀረ-ኢትዮጵያ አካሄድና ዓላማ በመቃወም የሕይወት ማስዋዕትነት የከፈሉ አመራር ነበሩ ወይ? ከነበሩስ እነማን ናቸው?
ገብረመድህን አርኣያ ከአስውትራሊያ
ከዚህ ቀጥለን የምንመለከተው ትኩረት ያልተሰጠውን ተሸፍኖ የነበረውን እና የህወሓት መሪዎች፣ በሕይወት ያሉትም የሞቱትም፣ ከወያኔ የተባረሩ አመራርም ጉዳዩ ወደ ውጭ እንዳይወጣ ተዳፍኖ እንዲቀር ከባድ ጥረት እያደረጉበት ያለውን ነው።

ሰላማዊ ሰልፉ ቢታገትም ፣ የተሳካ ሕዝባዊ ንቅናቄ ነበር! – ከአንድነት ፓርቲና ከ 33ቱ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ

1374061_10201496850957121_1380175466_nአንድነት ፓርቲ ከ33ቱ ፓርቲዎች ስብስብ ጋር በመሆን ዛሬ በአዲስ አበባ ከተማ ለማድረግ ያቀዱት ሰላማዊ ሰልፍ በገዢው ፓርቲ (መንግስት) ክልከላ ሠልፉ ሊደረግበት ወደነበረው መስቀል አደባባይም ሆነ በአማራጭ ነት ያቀረቡት 9 አደባባዮች እንዳይንቀሳቀስ ተደርጎ ከአንድነት ፓርቲ ጽ/ቤት እስከ ቀበና አደባባይ ባለው አስፋልት ላይ ቁጥሩ ከ80 ሺህ በላይ የአዲስ አበባ ነዋሪዎች በተገኙበት ደማቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ ተደርጓል፡፡ 
ለዚህ ደማቅ ሕዝባዊ ንቅናቄ የአንድነት ፓርቲና የ33ቱ ፓርቲዎች አመራሮች አባላትና ደጋፊዎች ያደረጉት ያላሰለሰ ጥረትና ሕዝቡ የመንግሥትን ፀጥታና የፖሊስ ኃይሎች ማስፈራራት አልፎ የላቀ አዎንታዊ ምላሽ ከፍተኛ ድርሻ አበርክተዋል፡፡ የአንድነት ፓርቲና የ33ቱ አመራር ህዝቡ ለሰጠው አመርቂ ምላሽ ከፍ ያለ ምስጋና እያቀረቡ፣በቀጣይ ለሚደረገው ወሳኝ ትግል ታላቅ የማበረታቻ እርሾ መሆኑን ያምናል፡፡ ከዚህም ሕዝቡ አመራር ካገኘ ለመብቱና ነፃነቱ ወደ ኋላ የማይል መሆኑንና በሕዝቡ ውስጥ ከፍተኛ የለውጥ ፍላጎት መኖሩን ያረጋገጥንበት፣ ትዕይንት ሲሆን በተጨማሪ ሠላማዊ ትግል በጋራ አመራር ከተያዘ ውጤታማ መሆኑን አምነናል፡፡
ሆኖም ከዚህ ሕዝባዊ ንቅናቄ የተማርነው ሌላ ነገር ቢኖር በአገራችን ያለውን የአስተዳደርና የህግ ጉዳይ ጥያቄ ውስጥ መውደቁንና ገዢው ፓርቲ በየትኛውም ደረጃ በሕዝብ በሚነሱ ጥያቄዎች በከፍተኛ ሥጋት ውስጥ የወደቀ መሆኑን ነው፡፡
የአዲስ አበባ መስተዳድርና የፌዴራሉ መንግሥት ለሰልፉ ዕውቅና ሰጥቻለሁ ቢልም የተለያዩ አስተዳደራዊ ደንቃራዎችን በመፍጠርና የማናውቃቸውን ቅድመ ሁኔታዎች በመፍጠር የቅስቀሳ ሥራችንን በማደናቀፍና ሕዝቡ ወደ ሰልፉ እንዳይወጣ በማድረግ በተግባር ሠልፍ የማይደረግባት አገር ለመፍጠር ሣይታክት ተግቶ ሰርቷል፡፡ ቀስቃሾችና አመራሮችን አስሯል መኪናዎችን አግቷል፡፡ በዚህ ውስጥ ማለፍ የተሣካ ሕዝባዊ ንቅናቄ በመፍጠራችን ከዚህ በመነሳት አንድነት ፓርቲና 33ቱ በጋራ በተጠናከረ መንገድ በመላው አገሪቱ ቀጣይና ተከታታይ ሕዝባዊ ንቅናቄ የማድረግ አስፈላጊነትን ተምረንበታል፡፡
ስለሆነም በአገር ቤትም ሆነ በውጭ አገር የምትገኙ የሠላማዊ ሕዝባዊ ንቅናቄ ደጋፊዎቻችን በሙሉ ለእስከዛሬው በድጋሚ እያመሰገንን ለቀጣዩ የጋራ ሥራችን እንደተለመደው ከጎናችን እንድትቆሙ ጥሪያችንን እናቀርባለን፡፡
አንድነት ፓርቲና 33ቱ ፓርቲዎች የተሰጠ መግለጫ
መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም603944_622133674503606_213601633_n994913_10201496979000322_682846221_n603944_622133674503606_213601633_n1374061_10201496850957121_1380175466_n

«እዚህ ያላችሁ አብዛኞቻችሁ የልጄቼ ልጆች ልትሆኑ ትችላላችሁ። ተስፋ የማድረግባችሁ ናችሁ» ብለዋል ዶር ነጋሶ

By:Minilik Salsawi 29.09.13

«ፖሊሶች ከአቅማቸው በላይ ነዉ። ሕገ መንግስትና በሕግ ሳይሆን በመመሪያ ነዉ የሚተዳደሩት። ሕዝቡ ሰላማዊ ሆኖም ከመርካቶ፣ ከሳሪስ፣ ከሜክሲሶ ሕዝቡ እንዳያልፍ ማድረጋቸው የፍርሃታቸው ጥግ የት እንደደረሰ የሚያሳይ ነዉ። የሰዉን ሁኔታ የተረዱ ይመስለኛል» አቶ ግርማ ሰይፉ

«ለአይንህ መጨረሻዉን የማታየው ሕዝብን ማየት ያሰደስታል። ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ በራሱ ግብ አይደለም። ላለፉት 3 ወራት በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል ስናደርግ የነበረው የመጀመሪያ ፌዝ አጠናቀናል። የመጀመሪያዉን ፌዝ አጠናቀቅን ስንል ፣ የትግሉ ሂደት ተጠናቀቀ ማለት አይደለም። ከመጣነዉ ይልቅ የሚቀረን እንደሚረዝም ነዉ የምናስበዉ» አቶ ሃብታሙ አያሌው። አቶ ሃብታሙ በቅርቡ በጸረ-ሽብር ሕጉ ዙሪያ በኢቲቪ በተደረገው ክርክር አንድነት ወክለዉ ቀርቦ የነበረ ወጣት የአንድነት አመራር አባል ነዉ።

AFP, Bloomberg News, AL JAzria ….የመሳሰሉ በርካታ የዉጭ ጋዜጠኞች ተገኝተዉ ነበር። ፖሊሶች መንገዱን መዝጋታቸውን ታዝበዋል። «ሰልፉ አልተፈቀደም እንዴ ? ከተፈቀደ ለምንድን ነው መንገድ የሚዘጉትም ? ህዝቡ እንዳይቀላቀል ለምን ያደርጋሉ ? » የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

የሰላማዊ ሰልፉ መርሃ ግብር ተጠናቋል። ምንም እንኳን አገዛዙ አይን ባወጣ መልኩ የሕዝብን መብት ቢረግጥ የአዲስ አበባ ሕዝብ ምን ያህል የሰለጠነ እንደሆነም አሳይቷል። አንድ ሰው ሳይጎዳ፣ አንዲት ጠጠር ሳይወረወር ሰልፍ በሚያስደንቅ ሁኔታ ተጠናቋል።

ከመርካቶ፣ ከሳሪስ ልደታ የሚመጡ መንገድ ተዘግቶ መምጣት አልቻሉም። በመቶ ሺህ የሚቆጠረዉ በቀበና አደባባይ የተሰበሰበው ሕዝብ በአጭሩ ከአንድ አካባቢ የተሰበሰበዉ ህዝብ ነዉ። ፖሊሶች መንገድ ባይዘጉና፣ ከሁሉም የአዲስ አበባ ክፍሎች ሕዝቡ እንዲያልፍ ቢደረግ ኖሮ ሚሊዮኖች ሊገኙ የሚችሉበት ሁኔታ ነበር።

ሰልፉን ለመዝጋት ዶር ነጋሶ ንግግር አድርገዋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት 70 አመታቸውን እንዳከበሩ የገለጹት ዶር ነጋሶ የተሰማቸዉን ከፍተኛ ደስታ ገልሰዋል።

«እዚህ ያላችሁ አብዛኞቻችሁ የልጄቼ ልጆች ልትሆኑ ትችላላችሁ። ተስፋ የማድረግባችሁ ናችሁ» ብለዋል ዶር ነጋሶ

በመጨረሻ የሰልፉ አዘጋጆች መንገዱን ለዘጉባቸው ፖሊስ ሰራዊቶች ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።

«አስተዳደሩ አዞናል። እባካችሁ ችግር ዉስጥ አትክተቱን»በሚል ፖሊሶች ልመና አድርገዋል። የአገዛዙ ፓርቲዎች ተደብቀዉ ህዝቡን እና ፖሊሲን ለማጋጨት እየሞከሩ ነዉ።(Minilik Salsawi)


«አስተዳደሩ አዞናል። እባካችሁ ችግር ዉስጥ አትክተቱን»በሚል ፖሊሶች ልመና አድርገዋል። የአገዛዙ ፓርቲዎች ተደብቀዉ

 ህዝቡን እና ፖሊሲን ለማጋጨት እየሞከሩ ነዉ። ግን የአንድነት አመራሮች በአገዛዙ ወጥመድ ዉስጥ ላለመግባት በማስተዋልና 

በእርጋታ ሕዝቡን እየመሩት ነዉ።

«ሃሩር የሆነ ጸሃይ ነዉ። ሕዝቡ ሂድ ስንለው ይሄዳል። ተቀመጥ ስንለው ይቀመጣል። በጣም ጨዋና ሰላማዊ ህዝብ ነዉ።» 

አቶ ሃብታሙ አያሌዉ

የሕዝብ ማእበል – ፖሊስ ሕዝቡ ሰልፍ እንዳይቀላቀል ሲያከላክል

መፈክሮች !

ሕዝብ አሸማቆ መግዛት አሸባሪነት ነዉ !

ኢሕአዴግነት ከኢትዮጵያዊነት አይበልጥም!

አንድ ናት አገራችን !

ሙስና የስርዓቱ መገለጫ ነዉ !

መብታችንን ከኢሕአዴግ አንጠብቀም !

ይሄ ስርዓት እስኪለወጥ ትግላችን ይቀጥላል።

ዶር ነጋሶ «ከቀበና ወደ ሚኒሊክ ሆስፒታል አድርገን ወደ ጃን ሜዳ እንድንቀሳቀስ ነዉ የሚፈልጉት። ይሄ ደግሞ 


አይሆንም።አደባባዩን ለመዞር እየሞከርን ነዉ። ከዚያ ወደ አራት ኪሎ እንዞራለን። ከፖሊስ ጋር ለመደባደብ አንፈልግም። እኛ 

ሰላማዊ ነን። » ዶር ነጋሶ የአንድነት ሊቀመንበር

«ይሄን ሰልፍ ፖሊሶች እየዘጉት ያለዉ በአስተዳደሩ ቀጥተኛ ትእዛዝ ነዉ። ተጠያቂዉ አስተዳደሩ ነዉ» አቶ ዳንኤል ተፈራ።

ቋጠሮ ፣ አቡጊዳ፣ ዘሃበሻ ፣ ኢትዮጵያን ሪቪው ድህረ ገጾች በአሁኑ ጊዜ አገር ቤት የሚደረገዉን ሰልፍ በስፋት እየዘገቡት ነዉ።


 የቃሌ፣ ሲቪሊቲ፣ ከረንት አፌር የፓልቶክ ክፍሎችም በቀጥታ ከአዲስ አበባ ስልክ እየደወሉ ሰልፉን እያስተላለፉ ነዉ።

Saturday, September 28, 2013

Water Wars: Egyptians Condemn Ethiopia's Nile Dam Project

As the Grand Ethiopian Renaissance Dam takes shape, tempers rise. 
Peter Schwartzstein in Cairo, National Geographic
September 28, 2013

"Ethiopia is killing us," taxi driver Ahmed Hossam said, as he picked his way through Cairo's notoriously traffic-clogged streets. "If they build this dam, there will be no Nile. If there's no Nile, then there's no Egypt."

Projects on the scale of the $4.7 billion, 1.1-mile-long (1.7-kilometer-long) Grand Ethiopian Renaissance Dam often encounter impassioned resistance, but few inspire the kind of dread and fury with which most Egyptians regard plans to dam the Blue Nile River.
Egypt insists Ethiopia's hydroelectric scheme amounts to a violation of its historic rights, a breach of the 1959 colonial-era agreement that allocated almost three-fourths of the Nile waters to Egypt, and an existential threat to a country largely devoid of alternative freshwater sources.
But what Egyptians regard as a nefarious plot by its historic adversary to control its water supply, Ethiopians see as an intense source of national pride and a symbol of their country's renewal after the debilitating famines of the 1980s and '90s.
"People are enthusiastic. They're excited, because no leader has tried such a project in Ethiopia's history," said Bitania Tadesse, a recent university graduate from the capital, Addis Ababa. "It's a big deal that is going to be beneficial to future generations."

“ግንቦት ሰባት” የጦር መሳሪያ ድጋፍ ከኤርትራ እንደሚያገኝ ገለፀ( by ማህሌት ፋሲል)


በኢትዮጵያ መንግስት አሸባሪ ተብለው ከተፈረጁት ድርጅቶች አንዱ የሆነው የ“ግንቦት ሰባት” አመራሮች ዶ/ር ብርሀኑ ነጋ እና አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ አሁን ያለውን የኢትዮጵያ መንግስት ከስልጣን ለማውረድ ለሚያደርጉት ሁለገብ ትግል ከኤርትራ መንግስት የጦር መሣሪያ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ሰሞኑን ለአሜሪካ ድምፅ ሬዲዮ በሰጡት መግለጫ አስታወቁ፡፡ ባለፈው ሰኞ ከሶስት መቶ በላይ ለሚሆኑ ኢትዮጵያውያን በአሜሪካ ቨርጂንያ ግዛት የድርጅታቸውን አቋም የገለፁት የድርጅቱ አመራር አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ፤ ከኤርትራ ፕሬዚዳንት ኢሳያስ አፈወርቅ ጋር በአካል ተገናኝተው እንደተነጋገሩና ከኤርትራ መንግስት ጥሩ ምላሽ ማግኘታቸውን ጠቁመው የመሳሪያ ድጋፍ እንደሚደረግላቸው ተናግረዋል፡፡ በቅርቡ ወደ ትጥቅ ትግል እንገባለን ያሉት አቶ አንዳርጎቸው ፅጌ፤ በስብሰባው ተሳታፊ ከነበሩ ሰዎች፤ ለምን ኤርትራን እንደመረጡና ሌላ አማራጭ ሀገር እንዳልፈለጉ ለቀረበላቸው ጥያቄ፤ “በአሁኑ ሰአት ባለው ሁኔታ ከኤርትራ የተሻለ ድጋፍ የሚሰጠን የለም” ሲሉ ምላሽ መስጠታቸውን የአሜሪካ ድምጽ ሬዲዮ ዘግቧል፡፡ “ግንቦት ሰባት” ከአልቃይዳ፣ አልሸባብ፣ ኦነግና ኦብነግ ጋር አሸባሪ ተብሎ በፓርላማ መፈረጁ የሚታወስ ሲሆን የድርጅቱ መሪዎች በሌሉበት የሞትና የእድሜ ልክ እስራት ተፈርዶባቸዋል፡፡

ከሠማይ ወረደ በተባለው መስቀል ላይ ቅዱስ ሲኖዶሡ ውሣኔ ይሰጣል(addis admass news)

ከሠማይ ወረደ በተባለው መስቀል ላይ ቅዱስ ሲኖዶሡ ውሣኔ ይሰጣልWritten by  አለማየሁ አንበሴበአቃቂ ቃሊቲ ገላን ጉራ ቅዱስ ገብርኤል ቤተክርስቲያን ባለፈው ነሐሴ ወር መጨረሻ ላይ ከሠማይ ወረደ ስለተባለው መስቀል ቅዱስ ሲኖዶስ ውሣኔ እስኪያስተላልፍ ህዝቡ በትዕግስት እንዲጠባበቅ የአዲስ አበባና የጅማ ሃገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ አሣሠቡ፡፡ “መስቀል ከሠማይ ወርዷል አልወረደም? ትክክለኛ ነው አይደለም?” የሚለውን ለመመለስ የግድ ቅዱስ ሲኖዶሡ ጉዳዩን መርምሮ ውሣኔ ሊያስተላልፍበት ይገባል ያሉት ብፁዕነታቸው፤ ይህን ለማድረግም ጉዳዩን ለቅዱስ ሲኖዶሱ ቋሚ አባላት እንዳሣወቁ ተናግረዋል፡፡ መስቀሉ እንደተባለው ከሠማይ የወረደ አለመሆኑ ከተረጋገጠም የቤተክርስቲያኒቱ ሃላፊዎች ይጠየቁበታል ብለዋል-ብፁዕነታቸው፡፡
መስቀሉ ከሠማይ ወረደ በተባለ በ4ኛው ቀን ነሐሴ 27 ቀን 2005 ከሠአት በኋላ ወደ ስፍራው በማቅናት ተገቢውን የፀሎት ስርአት ከካህናቱና ከቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች ጋር ካደረሡ በኋላ መስቀሉን ከወደቀበት መሬት አንስተው ወደ ቤተመቅደሡ እንዲገባ ማድረጋቸውን የገለፁት ብፁዕ አቡነ እስጢፋኖስ፤ መስቀሉ ከሠማይ ስለመውረዱ በአይናችን አይተናል ካሉት የቤተክርስቲያኒቱ አገልጋዮች እንደማንኛውም ሠው መስማታቸውን ለአዲስ አድማስ ገልፀዋል፡፡
መስቀሉን ከወደቀበት መሬት ያነሱት ብፁዕነታቸው፤ “መስቀሉ ያቃጥላል፤ ብርሃናማ ነፀብራቅ አለው” የሚባለውን አለማስተዋላቸውን ጠቁመው፤ “መስቀል የሚያቃጥል ሣይሆን የድህነት ሃይል ነው ያለው፣ የሚያቃጥል ቢሆን ኖሮ ከመሬት ላይ ማንሣት ባልተቻለ ነበር” ብለዋል፡፡ ወረደ የተባለውን መስቀል ለመመልከት ወደ ስፍራው የሚያቀኑ ምዕመናን ለምን እንዳይመለከቱት ተከለከለ የሚል ጥያቄ ያነሣንላቸው ብፁዕነታቸው፤ ጉዳዩ በቅዱስ ሲኖዶሡ ተጣርቶ ውሣኔ እስኪያገኝ ድረስ ህዝበ ክርስቲያኑ ጉዳዩን በጥሞና እንዲያጤነው በማሠብ ነው” ብለዋል፡፡
Read 31 times

በአንድነትና በ33ቱ ፓርቲዎች በጋራ የተሠጠ ጋዜጣዊ መግለጫ

  አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)             
UNITY FOR DEMOCRACY AND JUSTICE PARTY (UDJ)
    በማሰርና ማደናቀፍ የታጀበው ሰላማዊ ሰልፋችን በታቀደለት ዕለት በድምቀት ይካሄዳል!!
UDJአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ ለሶስት ወራት የሚቆይ ህዝባዊ ንቅናቄ በስትራቴጅው መሰረት በመጀመር፤ በመላው አገሪቱ የሚገኙ አባላቶቹንና ደጋፊዎቹን በማንቀሳቀስ ሕዝቡን ያሳተፈ ትግል በአዲስ አበባና ከአዲስ አበባ ውጭ በሚገኙ ዋና ዋና ከተሞች የተቃውሞ ሰልፎችንና ህዝባዊ ስብሰባዎችን ማከናወኑ የሚታወቅ ነው፡፡ የሚልዮኖች ድምጽ ለነፃነት በሚል መሪ ቃል የተጀመረው ይህ ህዝባዊ ንቅናቄ አራት መሰረታዊ ጥያቄዎችንና ወቅታዊ ጉዳዮችን ያነገበ ሲሆን እንደ ሁልጊዜውም ፓርቲው ሰላማዊነቱን በጠበቀ መልኩ ነገር ግን ሕጋዊ መብቱን ሳያስነካ፤ መከፈል የሚገባውን መስዋዕትነት በመክፈልና በቁርጠኝነት ንቅናቄውን በታቀደለት መሰረት ከአባላቱና አመራሩ ጋር በመሆን ለማከናወን ችሏል፡፡
አገሪቱን በማስተዳደር ላይ የሚገኘው ገዥ ሀይል በሰላማዊ ህዝባዊ ንቅናቄዎች ለሚነሱ ጥያቄዎች አፋጣኝ ምላሽ ከመስጠትና በተነሱ ጉዳዮች ዙሪያ ለመነጋገር በርን ከመክፈት ይልቅ ዙሪያ ጥምጥም በመሄድ ለጥያቄዎቹ አስተጋቢዎች የተለየ መልክ ለመፍጠር የሚያደርገው ሩጫ እንደተጠበቀ ሆኖ በህገ መንግስቱ በግልጽ የተቀመጡ ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ፣ የመሰብሰብና አቤቱታ የማቅረብ መብትን በአደባባይ እየጨፈለቀና እነዚህ መብቶች ይከበሩ ዘንድ የሚጠይቁ አባላቶቻችንን ከህግ አግባብ ውጪ በገፍ እያሰረም ቢሆን ህዝባችን ጋር ለመድረስና ተቃውሞ ድምፃችንን ከፍ አድርገን ማሰማት ችለናል፡፡

"I was called a terrorist yesterday "

Terrorism by “Anti-terrorism Law"

Lately, Meles Zenawi, the dictator in Ethiopia, has been rounding up dissidents, journalists, opposition party political leaders and members under a diktat known as “Anti-Terrorism Proclamation No. 652/2009”. This diktat approved on a 286-91 vote of the rubberstamp parliament is so arbitrary and capricious that Human Rights Watch concluded “the law could provide a new and potent tool for suppressing political opposition and independent criticism of government policy.”

Sakharov and the fight for a free press in Ethiopia

Ethiopian journalists Eskinder Nega and Reeyot Alemu. (Lennart Kjörling and IWMF)
Ethiopian journalists Eskinder Nega and Reeyot Alemu. (Lennart Kjörling and IWMF)
In 1968, Andrei Sakharov braved censorship and personal risk in the Soviet Union to give humanity an honest and timeless declaration of conscience. That same year, Ethiopia’s most prominent dissenter, Eskinder Nega, was born. In January 1981, a year into Sakharov’s exile in the closed city of Gorky, Reeyot Alemu, another fierce, Ethiopian free thinker, was born.
In considering both Eskinder, a veteran journalist and free speech activist, and Reeyot, a teacher and newspaper columnist, for the European Parliament’s Sakharov Prize, the selection committee is recognizing two uncompromising idealists and indomitable free thinkers who have stubbornly persisted in telling inconvenient truths about their government in a country silenced by fear.

Jaal Jaallannee Biqilaa: Nagaa Dhaamachuu Jaal Tasfahuun Camadaa (Oromo/Oromia)


Friday, September 27, 2013

Ethiopia: New punches to silence opposition

In late August Ethiopian police broke into the premises of the Blue party in Addis Ababa and arrested 60 people who were preparing a legal, peaceful demonstration. Several of those arrested were beaten by police, according to Amnesty International.
sz3c2179
2 June this year, thousands demonstrated in the streets of Addis Ababa, in the largest protests since the unrest in 2005. The protests were organized by the new opposition group Blue Party. Two months later the government to the party.

The  opposition has been very critical of Right to development in Ethiopia, a country that has had frequent visits by Norwegian coalition ministers. Relations with Ethiopia is one of the first development policy clarifications that a new socialist government must do.

10 American Foods that are Banned in Other Countries

(Sent by Yilma Tafere Tasew)

10-Foods
Americans are slowly waking up to the sad fact that much of the food sold in the US is far inferior to the same foods sold in other nations. In fact, many of the foods you eat are BANNED in other countries. Here, I’ll review 10 American foods that are banned elsewhere. (Click here to read)

ሀገር ማለት

faces-of-ethiopia

በዚህ ርእሰ ጉዳይ ላይ አስቀድሞ ደራሲ በዓሉ ግርማ በኋላም ዶ/ር በድሉ ዋቅጅራ ግጥሞቻቸውን ጽፈው ነበር፡፡ ሌላም የጻፈ ይኖራል፡፡ ነገር ግን እነኝህ የሥነ-ጽሑፍ ሰዎች ግጥሞቻቸውን ሲጽፉ የተቆነጸለ ወይም የተሳሳተ ትርጉም ሊያሰጥ በማያስችል ሁኔታ ግጥሞቻቸውን ባለመጻፋቸው እንደምገምተው እነሱም ሊሉ ባልፈለጉት መንገድ ተተርጉሞ የቅጥረኞች መጠቀሚያ እስከመሆን ድረስ በቃና ሕዝብን ለማደናገሪያ አገለገለ፡፡ ከሕዝቡ ጥቂት የማይባል ወገንም በመወናበድ ይሄንን የተሳሳተ [...]…read more
Via: Goolgule

በእስር ላይ የነበሩት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች ተፈቱ


በእስር ላይ የነበሩት የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮች
ዛሬ መስከረም 17 ቀን 2006 ዓ.ም. የቀድሞ የኢትዮጵያ ፕሬዘዳንት እና የአሁኑ የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ እንዲሁም በፓርላማ ብቸኛው የተፎካካሪ ፓርቲ ተወካይና የአንድነት ፓርቲ ምክትል ሊቀመንበር አቶ ግርማ ሰይፉን ጨምሮ በአዲስ አበባ አራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ የታሰሩት 26 የአንድነት አባላት ከሰዓታት ቆይታ በኋላ ተፈተዋል፡፡ በፖሊስ ተይዘው ወደጣቢያ የተወሰዱት የፓርቲው ዋና ፀሐፊ አቶ አስራት ጣሴ፣ የፓርቲው ሊቀመንበር ለመሆን በእጩነት የቀረቡትና የፋይናንስ ኃላፊ አቶ ተክሌ በቀለ፣ የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ አቶ ስዩም መንገሻ፣ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ዳንኤል ተፈራና ሌሎች አመራሮችም ነበሩበት፡፡
አመራሮቹ የፊታችን እሁድ መስከረም 19 ቀን 2006 ዓ.ም. ከጠዋቱ 2፡00 ሰዓት ጀምሮ ቀበና መድኃኔዓለም ቤተ ክርስቲያን ፊትለፊት ከሚገኘው የፓርቲው ዋና ጽህፈት ቤት አንድነት ፓርቲ ከ33 ተፎካካሪ ፓርቲዎች ጋር በመሆን ለጠሩት የተቃውሞ ህዝባዊ ሰላማዊ ሰልፍ በተለይ በአራዳ ክፍለ ከተማ በቅስቀሳ ላይ እያሉ መታሰራቸው ይታወቃል፡፡ ነገር ግን የአዲስ አበባ ከተማ መስተዳደር ለእሁዱ ሰላማዊ ሰልፍ እውቅና ቢሰጥም የከተማው ፖሊስ ለቅስቀሳ የሚሰማሩ የፓርቲው አባላትና ደጋፊዎችን በተደጋጋሚ ያለምንም በቂ ምክንያትና ክስ እያሰረ መፍታቱ አዲስ አይደለም፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ የአራዳ ክፍለ ከተማ ፖሊስ መምሪያ አመራሮቹንና አባላቱን ለምን እና በምን የህግ አግባብ ለሰዓታት እንዳሰረ ብንጠይቅም ታዘንነው ከማለት ውጭ ምላሽ ለመስጠት ፈቃደኛ አልሆኑም፡፡

በ10 ቀናት ውስጥ አንድ ባለ አንድ ፎቅ ተገነባ

መስከረም ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ አርክቴክቸር፣ ሕንጻ ግንባታ እና ከተማ ልማት ኢንስቲትዩት ከጀርመኑ ባዉሃዉስ ዩኒቨርሲቲ ኦፍ ዊመር እና ከደቡብ ሱዳኑ ጁባ ዩኒቨርሲቲ ጋር በመተባበር ከሶስቱም ዩኒቨርሲቲዎች በተውጣጡ ተማሪዎች አማካይነት 10 ቀናት ውስጥ  የባለ አንድ ፎቅ ተገጣጣሚ ሕንጻ ገነባ፡፡
ይህ በዓይነቱ አዲስ የሆነውን ቴክኖሎጂ በነገው ዕለት ይፋ ለማድረግ ፕሮግራም ተይዞአል፡፡ ቴክኖሎጂው በተለይ በጀርመን አገር የሚሰራበትና ጊዜና ወጪን በመቆጠብ ረገድ ወደር የሌለው ነው ተብሎለታል፡፡

በልደታ አካባቢ በሚገኘው የቴክኖሎጂ ፋክልቲ በነገው ዕለት በሚካሄደው የማስተዋወቂያ ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት እና የውጭ አገር አምባሳደሮችና  ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ይገኛሉ ተብሎአል፡፡የአዲስአበባ የቤቶች ልማት ድርጅት በዚህ ቀላል ቴክኖሎጂ በመጠቀም የከተማዋን የቤት ችግር የሚቀርፍበት አንድ አማራጭ ይሆናል ተብሎ የተገመተ ሲሆን ድርጅቱም ለቴክኖሎጂው ስኬት ድጋፍ ሲያደርግ መቆየቱ ታውቆአል፡፡

ከባድ የጦር መሳሪያዎችን የተሸከሙ መኪኖች ወደ ሰሜን ማቅናታቸው ተዘገበ


መስከረም ፲፯(አስራ ሰባት)ቀን ፳፻፮ / ኢሳት ዜና :-አይን እማኞች እንደገለጹት ባለፉት 3 ቀናት 30 በላይ የሚሆኑ ታንኮችን እና የጦር መሳሪያዎችን የጫኑ ከባድ ተሽከርካሪዎች ወደ ትግራይ ሰሜናዊ ክፍል አቅንተዋል።
መንግስት የጦር መሳሪያዎችን ለማንቀሳቀስ ለምን እንደፈለገ የታወቀ ነገር የለም። አንዳንድ ወገኖች እንደሚገምቱት በትግራይ አንዳንድ አካባቢዎች የሚንቀሳቀሱ አማጽያን የሚፈጥሩትን ስጋት ለመቋቋም ተብሎ የተወሰደ እርምጃ ሊሆን ይችላል።

በጉዳዩ ዙሪያ የመንግስት ባለስልጣናትን ለመነጋገር ያደረግነው ሙከራ አልተሳካም።

የአንድነት አመራር አባላት ጊዜያዊ እገታ(DW)

የኣንድነት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ ዓመራር አባላት የፊታችን እሁድ አዲስ ኣበባ ላይ ለጠሩት ሰልፍ ቅስቀሳ ለማድረግ እንዳልቻሉ ኣስታወቁ በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸናው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የሆኑትን አቶ ግርማ ሰይፉን ጨምሮ የፓርቲው ዓመራሮች ዛሬ ለተወሰኑ ሳዓታት በፓሊሶች ታግተው መለቀቃቸውን ፓርቲው ኣስታውቋል

የፓርቲው ሊቀመንበር / ነጋሶ ዲዳዳም ከትናንት በስቲያ በተመሳሳይ ሁኔታ ታግተው መለቀቃቸው ይታወሳል በኢትዮጵያ ፓርላማ ብቸናው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ እና የኣንድነት ለዲሞክራሲ እና ፍትህ ፓርቲ ከፍተና ዓመራር አቶ ግርማ ሰይፉ ዛሬ ከታገቱበት የአራዳ /ከተማ ፓሊሲ መምርያ ሆነው በእልክ ለዶቸቤሌ እንደገለጹት እሳቸውን ጨምሮ ኣጠቃላይ የፓርቲው ዓመራሮች እና ለቅስቀሳየተሰማሩ አባላቱ ባይታሰሩም በእሳቸው ኣባባል ታግተዋል አቶ ግርማ እንደሚሉት በኣሰራር ሰላማዊ ሰልፉ ተከልክለዋል በሰበብ ኣስባቡ ሌላ ጊዜ ሌላ ቦታ እየተባለ ግን ይነገራቸዋል ምክኒያታቸው ደግሞ የቅስቀሳ ፈቃድ የላችሁም የሚል ነው የቅስቀሳ ፈቃድ በራሱ ህገ ወጥ ነው ያሉት አቶ ግርማ ሰይፉ ፈቃዱንም ለማምጣት ፈቃድ ሰጪውም ሆነ የሚሰጥበት ቦታም ኣይታወቅም ብለዋል።
ይሁን እንጂ ፖሊስ የቅስቀሳ ቡድኑንም ሆነ የፓርቲውን ዓመራሮች ከማዋከብ ኣልታቀበም ያለመያዝ መብት ያላቸው አቶ ግርማ ሰይፉም ጭምር ከእገታውኣላመለጡም አቶ ግርማ እንደሚሉት ኣሁን የተያዘው ነገር እገታ ነው እሰሩን ብንልም ፈቃደና ኣይደሉም የሚሉት አቶ ግርማ ለጊዜው ቡድኑን በማገት እንቅስቃሴውን ማስተጎጎል ነው የተፈለገው ብለዋል በኣጠቃላይ ይላሉ አቶ ግርማ ሰይፉ የዚህ ዓይነቱ ኣሰራር በሰላማዊ መንገድ ለሚንቀሳቀሱት ኃይሎች በር እየዘጋ በህገ ወጥ መንገድ ለመታገል ለመረጡ ቡድኖች ጥርጊያ መንገድ ማመቻቸት ነውድምጽ አምስት አቶ ግርማ ሰይፉ በአቶ ግርማ ሰይፉ መግለጫ መሰረት ዛሬ ከቀትር በኃላ በሶስት ተሽከርካሪዎች አማካይነት የተሰማራው የቅስቀሳ ቡድን ታግቶ ቅስቀሳውም ተጨናግፈዋል ዓላማውም ሰላማዊ ሰልፉን ማሰናከል ነው ያሉት አቶ ግርማ ሰልፉን በተመለከተ ኣመራሩ ተሰብስቦ ፖለቲካዊ ውሳኔ እንደሚሰጥ ኣስታውቀዋል ይህንኑ ኣስመልክተው የበኩላቸውን ምላሽ እንዲሰጡን የኣራዳ /ከተማ ፖሊስ መምሪያን በስልክ ለማነጋገር ያደረግነው ተደጋጋሚ ሙከራ ኣልተሳካም
ጃፈር አሊ
ሂሩት መለሰ
AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

·        ቀን 27.09.2013