Sunday, September 29, 2013

«እዚህ ያላችሁ አብዛኞቻችሁ የልጄቼ ልጆች ልትሆኑ ትችላላችሁ። ተስፋ የማድረግባችሁ ናችሁ» ብለዋል ዶር ነጋሶ

By:Minilik Salsawi 29.09.13

«ፖሊሶች ከአቅማቸው በላይ ነዉ። ሕገ መንግስትና በሕግ ሳይሆን በመመሪያ ነዉ የሚተዳደሩት። ሕዝቡ ሰላማዊ ሆኖም ከመርካቶ፣ ከሳሪስ፣ ከሜክሲሶ ሕዝቡ እንዳያልፍ ማድረጋቸው የፍርሃታቸው ጥግ የት እንደደረሰ የሚያሳይ ነዉ። የሰዉን ሁኔታ የተረዱ ይመስለኛል» አቶ ግርማ ሰይፉ

«ለአይንህ መጨረሻዉን የማታየው ሕዝብን ማየት ያሰደስታል። ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ በራሱ ግብ አይደለም። ላለፉት 3 ወራት በተለያዩ የአገሪቷ ክፍሎች የሚሊዮኖች ድምጽ ለነጻነት በሚል ስናደርግ የነበረው የመጀመሪያ ፌዝ አጠናቀናል። የመጀመሪያዉን ፌዝ አጠናቀቅን ስንል ፣ የትግሉ ሂደት ተጠናቀቀ ማለት አይደለም። ከመጣነዉ ይልቅ የሚቀረን እንደሚረዝም ነዉ የምናስበዉ» አቶ ሃብታሙ አያሌው። አቶ ሃብታሙ በቅርቡ በጸረ-ሽብር ሕጉ ዙሪያ በኢቲቪ በተደረገው ክርክር አንድነት ወክለዉ ቀርቦ የነበረ ወጣት የአንድነት አመራር አባል ነዉ።

AFP, Bloomberg News, AL JAzria ….የመሳሰሉ በርካታ የዉጭ ጋዜጠኞች ተገኝተዉ ነበር። ፖሊሶች መንገዱን መዝጋታቸውን ታዝበዋል። «ሰልፉ አልተፈቀደም እንዴ ? ከተፈቀደ ለምንድን ነው መንገድ የሚዘጉትም ? ህዝቡ እንዳይቀላቀል ለምን ያደርጋሉ ? » የሚሉ ጥያቄዎችን አንስተዋል።

የሰላማዊ ሰልፉ መርሃ ግብር ተጠናቋል። ምንም እንኳን አገዛዙ አይን ባወጣ መልኩ የሕዝብን መብት ቢረግጥ የአዲስ አበባ ሕዝብ ምን ያህል የሰለጠነ እንደሆነም አሳይቷል። አንድ ሰው ሳይጎዳ፣ አንዲት ጠጠር ሳይወረወር ሰልፍ በሚያስደንቅ ሁኔታ ተጠናቋል።

ከመርካቶ፣ ከሳሪስ ልደታ የሚመጡ መንገድ ተዘግቶ መምጣት አልቻሉም። በመቶ ሺህ የሚቆጠረዉ በቀበና አደባባይ የተሰበሰበው ሕዝብ በአጭሩ ከአንድ አካባቢ የተሰበሰበዉ ህዝብ ነዉ። ፖሊሶች መንገድ ባይዘጉና፣ ከሁሉም የአዲስ አበባ ክፍሎች ሕዝቡ እንዲያልፍ ቢደረግ ኖሮ ሚሊዮኖች ሊገኙ የሚችሉበት ሁኔታ ነበር።

ሰልፉን ለመዝጋት ዶር ነጋሶ ንግግር አድርገዋል። ከሁለት ሳምንታት በፊት 70 አመታቸውን እንዳከበሩ የገለጹት ዶር ነጋሶ የተሰማቸዉን ከፍተኛ ደስታ ገልሰዋል።

«እዚህ ያላችሁ አብዛኞቻችሁ የልጄቼ ልጆች ልትሆኑ ትችላላችሁ። ተስፋ የማድረግባችሁ ናችሁ» ብለዋል ዶር ነጋሶ

በመጨረሻ የሰልፉ አዘጋጆች መንገዱን ለዘጉባቸው ፖሊስ ሰራዊቶች ምስጋናቸዉን አቅርበዋል።

No comments:

Post a Comment