Sunday, September 8, 2013

የሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት በዲፕሎማቱ ቢሮክራሲያዊ አሰራር ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው በመፈናቀላቸው ወላጆች ትላንት ሲቃውሞ ዋሉ !

በዲፕሎማቱ ቢሮክራሲያዊ አሰራር ከ1 ሺህ በላይ ተማሪዎች ከትምህርት ገበታቸው መፈናቀላቸውን ተከትሎ ወላጆች ትላንት ተቃውሞ ሲያሰሙ ዋሉ !
================================================
የሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በሪያድ የሚኖሩውን ኢትዮጵያዊ ማህበረስብ ልጆች በተመጣጣኝ ዋጋ ተቀብሎ በማስተናገድ የአካባቢው ስደተኛ ወገናችን የሚመካበት ት/ቤት መሆኑ ይታወቃል ። ለት/ቤቱ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ በክቡር ፕሪዝደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ የበላይ ጠባቂ ነት እንዲተዳደር ከማድረጉም በላይ በተለያዩ ግዜያቶች በ መንግስት ተሹመው የሚመጡ አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ለት/ቤቱ ታላቅ ግምት እና ቦታ በመስጠት ት/ቤቱ ተማሪ የመቀበል አቅሙን እንዲያሳድግ እና የኮሚኒቲው ማህበረሰብ የራሱ የሆነ ት/ቤት በኤንባስው ስም ገዝቶ ከኪራይ በማላቀቅ ት/ቤቱን የበለጠ በማሳደግ ወላጆች ልጆቻቸውን በተሻለ ወረሃዊ ክፍያ ማስተማር እንዲችሉ አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት ሲደርግ እንደነበር የት/ቤቱ ወላጆች ያስታውሳሉ። «ዛሬ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ »የሚለውን የጅሎች መፈክር አንግበው በመጡ ዲፕሎማቶች ባልታወቀ ምክንያት ት/ቤቱን ከኮሚኒተው ባለቤትነት ፈልቅቆ በማውጣት በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ት/ቤት በሚል ስያሜ በቦርድ እንዲተዳደር በማድረግ በት/ቤቱ ላይ አይን ያወጣ ዘረፋ በመፈሰም ላይ ይገኛል ። ት/ቤቱ ከእድገት ይልቅ ዛሬ ውድቀቱን በሚመኙለት ዲፕሎማቶች የትምህርት ጥራቱ እና የት/ቤቱ አጠቃላይ ሁለንተናዊ ገጽታ እያሽቆለቆለ የመጣው የኢትዮጵያው አምባሳደር መሃመድ ሃሰንን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማቶች እጅ ስለበዛበት እና እንዚሁ ዲፕሎማቶች ከሃገር ባስመጦቸው መምህራኖች እና የተለያዩ የት/ቤቱ አስተዳደሮች ት/ቤቱን ሙሉ ለሙሉ በመቋጣጠር ት/ቤት ላለፉት 5 አመታት ምንም አይነት ኦዲት ሳይደረግበት ከኮሚኒቲ ት/ቤትነት ይልቅ የተወሰኑ ሰዎች ኪስ ማደለቢያ በመሆኑ ምክንያት ለዚህ እንደተዳረገ ውስጥ ፡አውቂ ምንጮች ይገልጻሉ። 

ይህ ባለበት ሁኔታ ሰሞኑንን የሳውዲ አረቢያ መንግስት መኖሪያ ፈቃድ « ኢቃም » የሌለው መማር እንዳምይችል ያወጣውን አዋጅ ተከትሎ በኤንባሲው ዲፕሎማት የተመረጠው የት/ቤቱ ህገወጥ፡ ቦርድ የሳውዲ መንግስት ት/ሚኒስቴር ካስቀመጠው ደንብ እና ስረአት በላይ በተመዝጋቢ ተማሪዎች ላይ ተጨማሪ መመሪዎችን በማውጣት ከ1 ሺህ በላይ ህጻናትን ከትምህረት ገበታቸው በማፈናቀል በተቀሩት ተማሪዎች ላይ የመጸሃፍ እና ተጨማሪ ወረሃዊ ክፍያዎችን ወላጆች እንዲከፍሉ በማስገደድ በት/ቤቱ የመማር መስተማር ሂደቱን በማስተጓል ላይ እደሚገኙ ወላጆች ይገልጻሉ። 

ዛሬ የት/ቤቱን መከፈት ተከትሎ ልጆቻቸው በሰው ሃገር ያለትምህርት የቀሩባቸው ወላጆች ብሷታቸውን ለመግለጽ፡ የት/ቤቱን ቅጥር ግቢ በተቃውሞ አጠለቅልቀውት ውለዋል። አንዳንድ ወላጆች ልጆቻቸው የመኖሪያ ፈቃድ እና ህጋዊ የኢትዮጵያ ፕስፖርት እያላቸው የእናት ፓስፖርት ከሌለ መመዝገብ አትችሉም ተብለው ልጆቻቸው ያለትምህርት እንዲቀሩ መደረጉ ፍተሃዊነት እና ወገንዊነት የጎደለው አሰራር መሆኑንን ገልጸዋል። አብዛኛው ወላጆቻቸው የልጆቻቸው ከትምህርት መፈናቀልን ተከትሎ ባሰሙ ተቃውሞ ላይ እንባ እየተናነቃቸው ሲነገሩ እንደነበር ተስተውሏል ። አንድ ወላጅ እኔ ከእንግዲህ ልጆቼን የመስተማር አቅም የለኝም በማለት ብሷታቸውን ሲገልጹ የልጆቸው ያለትምህርት መቅረት ሃገርን እና ወገንን እንደሚጎዳ ጠቅሰው ዲፕሎማቶቻችን በልጆቻችን ላይ እንዲህ የጨከኑ« በዳዎቹ » ምንሊያደጉን እንደሚችሉ ፍረዱ ብለው አይሌ የስብሰባውን ተካፋይ አንባ አራጭተዋል። በወቅቱ የተማሪውችን ብሷት ለማድመጥ የመጡት የት/ቤቱ ረዕስ መምህር ሲገልጹ ወላጆች በችግሮቻቸው ዙሪያ ከመስተዳድሩ ጋር ለመነጋገር በዚህ መልኩ መምጣታቸው ተግቢ መሆኑን አድንቀው ጉዳዩ እዚህ ደረጃ ይደርሳል ብለው እሰብው እንዳልነበረ እና ባላቸው መረጃ መሰረት ከት/ቤቱ የትምህርት ገበታ የተፈናቀሉት በአብዛኛው ጀማሪ ህጻናት መሆናቸው ጠቅሰው የ8ኛ ክፍል ተማሪ እና ከዛበላይ ዘንድሮ ማትሪክ ለመውሰድ እይተማሩ ያሉ ነባር ተማሪዎች መፈናቀላቸውን አያውቁ እንደነበር ለተሰብሳቢው በመግለጻቸው በረዕሰ መምህሩ አባብል የተበስጩ ወገኖች ት/ቤቱ በንደዚህ አይነት ሰው መመራቱ አስዝኖቸዋል። በመጨረሻ ኪትዮጵያ ኤንባሲ የዲያስፖራው ተወካይ አቶ ተመስገን ይመር እና አቶ ዘላለም ወላጆች ላቀረቧቸው 4 አጥያቄዎች መልስ ለመስጠጥ 1/ የት/ቤቱ ረዕሰ ምመህር 2/ የት/ቤቱ ቦርድ ሊቀመንበር 3/ 11 አባላት ያሉት የወላጆች ኮሚቴ ከኢትዮጵያ ኤንባሲ 2 ዲፕሎማቶች የሚገኙበት ሰፊ ውይይት ዛሬ በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ እንደሚካሄድ ተገልጾል። 

ወላጆቹ ያቀረቦቸው ጥያቄዎች 
1/ የኮሚኒትው ት/ቤት ወደ ቀድሞው ይዞታው ይመለስ 
2/ ከትምህረት ገበታቸው የተፈናቀሉ ተማሪዎች ያለ ምንቅድመሁኔታ ወድ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ 
3/ በተለያዩ ምክንያቶች የት/ቤቱ መስተዳደር እና ቦርድ በወላጆች ላይ የሚፈጽመው ብዝበዛ ይብቃ 
4/ ዘንድሮ የወድቁትን ተማሪዎች ታሳቢ በማድረግ በት/ቤቱ የአስተዳደር እና የመማር መስተማር «የትምህርት ጥራት» ችግር ይቀረፍ !

Ethiopian Hagere ከሳውዲ አረቢያ ጅዳ ( በዋዲ )







የሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ት/ቤት ላለፉት ሁለት አስርት አመታት በሪያድ የሚኖሩውን ኢትዮጵያዊ ማህበረስብ ልጆች በተመጣጣኝ ዋጋ ተቀብሎ በማስተናገድ የአካባቢው ስደተኛ ወገናችን የሚመካበት ት/ቤት መሆኑ ይታወቃል ። ለት/ቤቱ መንግስት ትኩረት ሰጥቶ በክቡር ፕሪዝደንት ግርማ ወልደጊዮርጊስ የበላይ ጠባቂ ነት እንዲተዳደር ከማድረጉም በላይ በተለያዩ ግዜያቶች በ መንግስት ተሹመው የሚመጡ አምባሳደሮች እና ዲፕሎማቶች ለት/ቤቱ ታላቅ ግምት እና ቦታ በመስጠት ት/ቤቱ ተማሪ የመቀበል አቅሙን እንዲያሳድግ እና የኮሚኒቲው ማህበረሰብ የራሱ የሆነ ት/ቤት በኤንባስው ስም ገዝቶ ከኪራይ በማላቀቅ ት/ቤቱን የበለጠ በማሳደግ ወላጆች ልጆቻቸውን በተሻለ ወረሃዊ ክፍያ ማስተማር እንዲችሉ አቅም ለመፍጠር ከፍተኛ ጥረት ሲደርግ እንደነበር የት/ቤቱ ወላጆች ያስታውሳሉ። «ዛሬ የአባትህ ቤት ሲዘረፍ አብረህ ዝረፍ »የሚለውን የጅሎች መፈክር አንግበው በመጡ ዲፕሎማቶች ባልታወቀ ምክንያት ት/ቤቱን ከኮሚኒተው ባለቤትነት ፈልቅቆ በማውጣት በሪያድ አለም አቀፍ የኢትዮጵያ ት/ቤት በሚል ስያሜ በቦርድ እንዲተዳደር በማድረግ በት/ቤቱ ላይ አይን ያወጣ ዘረፋ በመፈሰም ላይ ይገኛል ። ት/ቤቱ ከእድገት ይልቅ ዛሬ ውድቀቱን በሚመኙለት ዲፕሎማቶች የትምህርት ጥራቱ እና የት/ቤቱ አጠቃላይ ሁለንተናዊ ገጽታ እያሽቆለቆለ የመጣው የኢትዮጵያው አምባሳደር መሃመድ ሃሰንን ጨምሮ የተለያዩ ዲፕሎማቶች እጅ ስለበዛበት እና እንዚሁ ዲፕሎማቶች ከሃገር ባስመጦቸው መምህራኖች እና የተለያዩ የት/ቤቱ አስተዳደሮች ት/ቤቱን ሙሉ ለሙሉ በመቋጣጠር ት/ቤት ላለፉት 5 አመታት ምንም አይነት ኦዲት ሳይደረግበት ከኮሚኒቲ ት/ቤትነት ይልቅ የተወሰኑ ሰዎች ኪስ ማደለቢያ በመሆኑ ምክንያት ለዚህ እንደተዳረገ ውስጥ ፡አውቂ ምንጮች ይገልጻሉ። 


ይህ ባለበት ሁኔታ ሰሞኑንን የሳውዲ አረቢያ መንግስት መኖሪያ ፈቃድ « ኢቃም » የሌለው መማር እንዳምይችል ያወጣውን አዋጅ ተከትሎ በኤንባሲው ዲፕሎማት የተመረጠው የት/ቤቱ ህገወጥ፡ ቦርድ የሳውዲ መንግስት ት/ሚኒስቴር ካስቀመጠው ደንብ እና ስረአት በላይ በተመዝጋቢ ተማሪዎች ላይ ተጨማሪ መመሪዎችን በማውጣት ከ1 ሺህ በላይ ህጻናትን ከትምህረት ገበታቸው በማፈናቀል በተቀሩት ተማሪዎች ላይ የመጸሃፍ እና ተጨማሪ ወረሃዊ ክፍያዎችን ወላጆች እንዲከፍሉ በማስገደድ በት/ቤቱ የመማር መስተማር ሂደቱን በማስተጓል ላይ እደሚገኙ ወላጆች ይገልጻሉ።

ዛሬ የት/ቤቱን መከፈት ተከትሎ ልጆቻቸው በሰው ሃገር ያለትምህርት የቀሩባቸው ወላጆች ብሷታቸውን ለመግለጽ፡ የት/ቤቱን ቅጥር ግቢ በተቃውሞ አጠለቅልቀውት ውለዋል። አንዳንድ ወላጆች ልጆቻቸው የመኖሪያ ፈቃድ እና ህጋዊ የኢትዮጵያ ፕስፖርት እያላቸው የእናት ፓስፖርት ከሌለ መመዝገብ አትችሉም ተብለው ልጆቻቸው ያለትምህርት እንዲቀሩ መደረጉ ፍተሃዊነት እና ወገንዊነት የጎደለው አሰራር መሆኑንን ገልጸዋል። አብዛኛው ወላጆቻቸው የልጆቻቸው ከትምህርት መፈናቀልን ተከትሎ ባሰሙ ተቃውሞ ላይ እንባ እየተናነቃቸው ሲነገሩ እንደነበር ተስተውሏል ። አንድ ወላጅ እኔ ከእንግዲህ ልጆቼን የመስተማር አቅም የለኝም በማለት ብሷታቸውን ሲገልጹ የልጆቸው ያለትምህርት መቅረት ሃገርን እና ወገንን እንደሚጎዳ ጠቅሰው ዲፕሎማቶቻችን በልጆቻችን ላይ እንዲህ የጨከኑ« በዳዎቹ » ምንሊያደጉን እንደሚችሉ ፍረዱ ብለው አይሌ የስብሰባውን ተካፋይ አንባ አራጭተዋል። በወቅቱ የተማሪውችን ብሷት ለማድመጥ የመጡት የት/ቤቱ ረዕስ መምህር ሲገልጹ ወላጆች በችግሮቻቸው ዙሪያ ከመስተዳድሩ ጋር ለመነጋገር በዚህ መልኩ መምጣታቸው ተግቢ መሆኑን አድንቀው ጉዳዩ እዚህ ደረጃ ይደርሳል ብለው እሰብው እንዳልነበረ እና ባላቸው መረጃ መሰረት ከት/ቤቱ የትምህርት ገበታ የተፈናቀሉት በአብዛኛው ጀማሪ ህጻናት መሆናቸው ጠቅሰው የ8ኛ ክፍል ተማሪ እና ከዛበላይ ዘንድሮ ማትሪክ ለመውሰድ እይተማሩ ያሉ ነባር ተማሪዎች መፈናቀላቸውን አያውቁ እንደነበር ለተሰብሳቢው በመግለጻቸው በረዕሰ መምህሩ አባብል የተበስጩ ወገኖች ት/ቤቱ በንደዚህ አይነት ሰው መመራቱ አስዝኖቸዋል። በመጨረሻ ኪትዮጵያ ኤንባሲ የዲያስፖራው ተወካይ አቶ ተመስገን ይመር እና አቶ ዘላለም ወላጆች ላቀረቧቸው 4 አጥያቄዎች መልስ ለመስጠጥ 1/ የት/ቤቱ ረዕሰ ምመህር 2/ የት/ቤቱ ቦርድ ሊቀመንበር 3/ 11 አባላት ያሉት የወላጆች ኮሚቴ ከኢትዮጵያ ኤንባሲ 2 ዲፕሎማቶች የሚገኙበት ሰፊ ውይይት ዛሬ በኢትዮጵያ ኮሚኒቲ ግቢ እንደሚካሄድ ተገልጾል።

ወላጆቹ ያቀረቦቸው ጥያቄዎች
1/ የኮሚኒትው ት/ቤት ወደ ቀድሞው ይዞታው ይመለስ
2/ ከትምህረት ገበታቸው የተፈናቀሉ ተማሪዎች ያለ ምንቅድመሁኔታ ወድ ትምህርት ገበታቸው ይመለሱ
3/ በተለያዩ ምክንያቶች የት/ቤቱ መስተዳደር እና ቦርድ በወላጆች ላይ የሚፈጽመው ብዝበዛ ይብቃ
4/ ዘንድሮ የወድቁትን ተማሪዎች ታሳቢ በማድረግ በት/ቤቱ የአስተዳደር እና የመማር መስተማር «የትምህርት ጥራት» ችግር ይቀረፍ !

Ethiopian Hagere ከሳውዲ አረቢያ ጅዳ ( በዋዲ )


No comments:

Post a Comment