Tuesday, December 31, 2013

የማዕድን ሥራዎች አዋጅ ፀደቀ

       01 JANUARY 2014 ተጻፈ በ  
 አዋጁ የመንግሥትን ነፃ ድርሻ ከፍ ያደርጋል

የማዕድን ሥራዎች አዋጅን ለማሻሻል የቀረበው ረቂቅ አዋጅ ፀደቀ፡፡ አዋጁ በማዕድን ዘርፍ በሚሰማሩ ድርጅቶች ላይ መንግሥት የሚኖረውን ድርሻ ከፍ ያደርጋል፡፡

በሥራ ላይ የሚገኘው አዋጅ መንግሥት በማዕድን አምራች ኩባንያዎች ላይ ያለምንም ክፍያ ከ0.1 በመቶ እስከ አምስት በመቶ የአክሲዮን ድርሻ እንዲኖረው ቢፈቅድም፣ ታኅሣሥ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ተሻሽሎ የፀደቀው አዋጅ ግን የመንግሥት ድርሻ አምስት በመቶ እንዲሆንና ከዚህ ዝቅ እንዳይል ደንግጓል፡፡
የአነስተኛ ወይም የከፍተኛ ደረጃ የማዕድን ሥራ ፈቃድ አግኝቶ የተሰማራ ድርጅት ለንግድ በሆነ መጠን ማዕድን ማምረት ከጀመረበት ቀን አንስቶ ለመጀመሪያዎቹ ሦስት ወራት ሊያሠሩት የሚችሉ ማናቸውንም አላቂ ዕቃዎች፣ ከቀረጥና ታክስ ነፃ ማስገባት እንደሚችል በፀደቀው አዋጅ ተካቷል፡፡

ማንኛውም ማዕድን አምራች ያመረተውን መጠን እያንዳንዱ ወር ባለቀ በአሥር ቀናት ውስጥ ፈቃድ ለሰጠው አካል ማሳወቅ እንደሚገባው፣ ላኪዎች ደግሞ ያመረቱትን ማዕድን ሩብ ዓመት በተፈጸመ ሰላሳ ቀናት ባልበለጠ ጊዜ ውስጥ መሸጥና ማሳወቅ እንደሚገባቸው ይደነግጋል፡፡ 

ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሐሙስ በአቶ መላኩ ፈንታ ጉዳይ ላይ ለመወያየት ይሰበሰባል

በከባድ የሙስና ወንጀል ተጠርጥረው ላለፉት ስምንት ወራት በእስር ላይ የሚገኙት፣ በቀድሞው የኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር በአቶ መላኩ ፈንታ ጉዳይ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ፣ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ሐሙስ እንደሚሰበሰብ ፍርድ ቤት ትናንትና አስታወቀ፡፡
የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ 15ኛ ወንጀል ችሎት፣ የአቶ መላኩ ፈንታን ክስ የማየት ሥልጣን ያለው ፍርድ ቤት የትኛው እንደሆነ ሕገ መንግሥታዊ ትርጉም በመስጠት እንዲያሳውቀው ለሕገ መንግሥት አጣሪ ኮሚሽን ትዕዛዝ ማስተላለፉን መዘገባችን ይታወሳል፡፡
በመሆኑም ሕገ መንግሥት አጣሪ ኮሚሽን የፍርድ ቤቱን ትዕዛዝ ተግባራዊ ማድረጉንና ያጣራውን ጉዳይ ተጠሪ ለሆነበት ለፌዴሬሽን ምክር ቤት ማቅረቡን ለፍርድ ቤቱ ማሳወቁን ተከትሎ፣ ፌዴሬሽን ምክር ቤት ከሕገ መንግሥት አጣሪ ኮሚሽን በቀረበለት ሪፖርት ላይ ውሳኔ አሳልፎ እንዲያሳውቀው ለማክሰኞ ታኅሣሥ 22 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ ሰጥቶ ነበር፡፡

የፌዴሬሽን ምክር ቤት ለፍርድ ቤቱ ታኅሣሥ 15 ቀን 2006 ዓ.ም. በጻፈው ደብዳቤ፣ ከሕገ መንግሥት አጣሪ ኮሚሽን አቶ መላኩ ፈንታን አስመልክቶ በደረሰው ጉዳይ ላይ ተወያይቶ ውሳኔ ለማሳለፍ ለሐሙስ ታኅሣሥ 24 ቀን 2006 ዓ.ም. ቀጠሮ መያዙን እንዳሳወቀው ፍርድ ቤቱ ገልጿል፡፡ በመሆኑም ፌዴሬሽን ምክር ቤት ውሳኔውን ለጥር 5 ቀን 2006 ዓ.ም. እንዲያቀርብ ቀጠሮ ሰጥቷል፡፡

ወቅታዊ መልዕክት - በስደት ከሚገኙት ፓትርያርክ ብጹዕ ወቅዱስ አቡነ መርቆሬዎስ


መልዕክቱን ለማንበብ እዚህ ላይ ይጫኑ

Ethiopian Reporter’s journalist sentenced to two-year-and-nine-month imprisonment

December 31, 2013, ADDIS ABABA, Ethiopia (AP) — The Committee to Protect Journalists is urging the release of an Ethiopian journalist who was sentenced to more than two years in jail on the charge of spreading false rumors.
The watchdog group said Asfaw Berhanu, a former contributor to the private paper The Reporter, was convicted on Dec. 25 of charges stemming from a news story he wrote saying three government officials had been removed from their posts. An Ethiopian court sentenced him to two years and nine months in jail.
Berhanu’s paper later retracted the story and then fired him, the group said.
Ethiopia is among the world’s top jailers of journalists, says the journalists’ committee.
The Ethiopian government is accused of criminalizing the coverage of any group the government deems to be terrorists, including opposition political parties.
Source: AP

Nairobi, December 30, 2013 (CPJ)An Ethiopian court convicted a journalist on December 25 on the charge of spreading false rumors and sentenced him to two years and nine months in prison, according to local journalists.
The First Instance Court in Hawassa, capital of the state of Southern Nations, Nationalities and Peoples’ Regions, convicted Asfaw Berhanu, former contributor to the private bilingual paper The Reporter, in connection with a September 4 article he wrote for the publication that claimed three state government officials had been removed from their posts, local journalists said.
The officials had not actually been dismissed from their posts, the sources said. TheReporter issued a front-page retraction in its next edition and dismissed Asfaw, ReporterManaging Director Kaleyesus Berkeley said.
Asfaw is being held in Hawassa Prison, local journalists said. He plans to appeal the sentence, the same sources said.
“Asfaw Berhanu should not be jailed for making a mistake, especially after the Reporterapologized and issued a retraction,” said CPJ East Africa Representative Tom Rhodes. “Authorities should release Asfaw from prison immediately.”
On October 10, three policemen visited The Reporter office in Addis Ababa and arrested Managing Editor Melaku Demissie, taking him for questioning in connection with the September 4 news report, according to local journalists and news reports. The police commissioner ordered his release the same day, Melaku told CPJ.
Source: CPJ


Reporter’s stringer sentenced to two-year-and-nine-month imprisonment

December 28, 2013 (The Reporter) — The Southern Nations, Nationalities and Peoples Regional State, Hawassa Town First Instance Court sentenced Asfaw Berhanu, former stringer of Reporter, to a two-year-and-nine-month prison term on Wednesday December 25 for spreading false rumors.
Asfaw was charged on two counts. The first relates to a news report that was published on the front page of the September 4, 2013 issue of the Amharic-language Reporter newspaper stating that three deputy presidents of the regional state were removed from their posts while the second accuses him of failing to return government properties that came into his possession while he was working in the regional state’s Trade and Industry Bureau including a laptop, a field bag and a calculator.
Asfaw was convicted of the first charge only. He was acquitted of the second.
On October 10, 2013 Melaku Demissie, the Managing Editor of the Amharic Reporter, was arrested and taken to Hawassa for questioning in connection with the aforementioned news report and released the day after without being charged.
The news report was retracted on the next edition of the newspaper.
It was also reported that the Hawassa stringer, who wrote the erroneous story which caused this sentence faced administrative measures after the editorial team discovered that the story was in fact wrong.

ኢህአዴግ በሶስት ድርጅቶች ላይ አዲስ ዘጋቢ ፊልም እያዘጋጀ መሆኑ ተሰማ

ኢህአዴግ በሶስት ድርጅቶች ላይ አዲስ ዘጋቢ ፊልም እያዘጋጀ መሆኑ ተሰማ
በመሰራት ላይ ያለው አዲስ ፊልም ኦነግ ፤ ኦብነግ እና ግንቦት ሰባትን በሽብርተኝነት የሚያወግዝ ነው።
ኢህአዴግ በዚህ ሰአት ፊልሙን ለምን ለመስራት እንደፈለገ ግልጽ የሆነ ነገር የለም። አንዳንዶች እንደሚገምቱት ከሆነ ግን ገዢው ፓርቲ በድርጅቶች እንቅስቃሴ ስጋት እየገባው ነው።
እየተሰራ ባለው ፊልም ውስጥ ኢሳትንም ለመወንጀል እየታሰበ መሆኑን ምንጮች አስታውቀዋል። ዘጋቢ ፊልሙ እስካሁን ባለመጠናቀቁ እና የመጨረሻውን የአርትኦት ይለፍ ባለማግኘቱ በይዘቱ ላይ ሙሉ አስተያየት ለመስጠት አላስቻለም። 
ኢህአዴግ ሶስቱን ድርጅቶች አሸባሪ ብሎ ከሰየማቸው ጀምሮ ተከታታይ ዘጋቢ ፊልሞችን ሲሰራ ቆይቷል።
Source:ESAT

ኢትዩጵያ ህጻናትን ወደ ውጭ በጉዲፈቻ ስም በመላክ ከአፍሪካ ቀዳሚ መሆኑዋና መረጃዎች አመለከቱ


ታህሳስ ፳፪( ሃያ ሁለት )ቀን ፳፻፮ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-በቅርቡ የወጡ መረጃዎች እንዳሳዩት በአፍሪካ ባለፉት 6 ዓመታት በጉዲፈቻ ስም ወደ ውጭ ከተላኩት 34 ሺ 342 ህጻናት ውስጥ 63 በመቶ ወይም 21 ሺ 365 ሰዎችን በመላክ ቀዳሚ ናት።

በሃገሪቱ በሰራተኛ እና ማህበራዊ ጉዳይ ፈቃድ የተሰጣቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ጉዳይ አስፈፃሚ የጉዲፊቻ ደላሎች ተበራክተዋል፡፡ በአብዛኛው ለጉዲፈቻ በሚቀርቡ ህፃናት የህይዎት ታሪክ ላይ የሚጻፈው ” ተጥለው የተገኙ ወይም ወላጆቻቸውን  በህይዎት ያጡ ” የሚል በመሆኑ በልጆቹ ህይወት ላይ ከፍተኛ ተጽእኖ አለው።

አትሌቷና አሰልጣኟን ያፋጠጠው ‹‹ትዳር››

jjjከሁለት ዓመት ወዲህ ብቅ ካሉ ወጣት ሴት አትሌቶች መካከል በውጤታማነት የምትጠቀሰው ቡዜ ድሪባ ናት፡፡ ለመጀመርያ ጊዜ በኢንተርናሽናል የመም መድረክ ላይ ብቅ ያለችው በ2004 ዓ.ም. በዱባይና በሞናኮ ከተሞች በተደረጉት የ1500 ሜትርና የ3000 ሜትር ሩጫ ውድድሮች ነው፡፡
ከመካከለኛ ርቀት ወደ ረዥም ርቀት 5000 ሜትር ለመሸጋገርም ጊዜ አልወሰደባትም፡፡ ሐቻምና በባርሴሎናው የዓለም ወጣቶች ሻምፒዮና በ5000 ሜትር አንደኛ በመሆን የወርቅ ሜዳሊያ በማጥለቋ ተተኪነቱን እንደምትይዝ ተስፋ ተጥሎባታል፡፡ለዚህም አምና በተካሄደው የሞስኮው ዓለም ሻምፒዮና መሠረት ደፋር ባሸነፈችበት የ5000 ሜትር ውድድር ጠንካራ ተፎካካሪ ሆና በመቅረቧ አምስተኛነት ለመያዝ አስችሏታል፡፡ በዓለም ወጣቶች አገር አቋራጭ ሻምፒዮና የተጀመረው የሩጫዋ ጉዞ በዓለም ሻምፒዮናና በአህጉራዊ ውድድሮች ተጠናክሮ እንዲቀጥል ለማድረግ ለዘንድሮ ውድድሮች ከተመረጡትና ጥሪ ከተደረገላቸው አትሌቶች አንዷ ብትሆንም ልትገኝ አልቻለችም፡፡

አርቲስት ዳንኤል ተገኝ ታሰረ



(ዘ-ሐበሻ) በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ይተላለፍ በነበረው ገመና ድራማ የዶ/ር ምስክርን ገፀ ባህርይ ወክሎ የተወነውና በተለያዩ ፊልሞች ላይ የተወነው አርቲስት ዳንኤል ተገኝ መታሰሩን የዘሐበሻ ዘጋቢዎች ከአዲስ አበባ ገለጹ። አርቲስቱ የታሰረው በካራማራ ፖሊስ ጣቢያ ሲሆን ዛሬ ፍ/ቤት ይቀርባል፡፡ የጊዜ ቀጠሮ ተጠይቆበት ለቀጣዮቹ 14 ቀናት እስር ቤት እንደሚቆይም ይጠበቃል፡፡
የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች የአርቲስቱን የክስ መዝገብ በመጥቀስ እንደዘገቡት ዳንኤል የታሰረበት ምክንያት አንዲት ባለትዳር ሴትን ከሌላ ወንድ ጋር ስትሳሳሚ ፎቶ አንስቼሻለሁ ይህንንም ፎቶ በፌስ ቡክ አለቀዋለሁ ብሎ በስልክና በአካል በማስፈራራቱ ነው፡፡ አርቲስቱ ከዚህችው ወ/ሮ ፊልም እሰራለሁ ብሎ 500 ሺ ብር እንደተቀበለና በማጭበርበር ክስ እንደቀረበበት በተለያዩ ሚዲያዎች በዘገቡ ይታወቃል፡፡( ስለዚሁ ጉዳይ ባለፈው ቅዳሜ ለንባብ የበቃው ቁም ነገር መፅሄት ሁለቱንም ወገኖች ማነጋገሩ ይታወቃል) ሰለጉዳዩ ተከታትለን እናቀርባለን።

Monday, December 30, 2013

በተቀነባበረ የመብራት ሀይል ሙስና ኢትዮጵያ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ እንድታጣ ተደረገ


በተቀነባበረ የመብራት ሀይል ሙስና ኢትዮጵያ ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ እንድታጣ ተደረገ
በኢትዮጵያ ኤለክትሪክ ሀይል ኮርፖሬሽን ውስጥ በታየው ከፍተኛ የሙስና ወንጀል አገሪቱ ግማሽ ቢሊዮን የሚጠጋ ገንዘብ አጥታለች። ይህንን የሙስና አሰራር የተቃወሙት ስራ አስኪአጁ አቶ ምህረት ደበበ በመጨረሻ ከስልጣናቸው ተነስተዋል።
የህወሃቱ ነባር ታጋይ፣ የደህንነት ምክትል ሃላፊ ፣ በአሁኑ ጊዜ በም/ል ጠቅላይ ሚኒስትር ማእረግ የኢኮኖሚ ክላስተር አስተባባሪ እና የመብራት ሃይል የቦርድ ሰብሰባ የሆኑት ዶ/ር ደብረ ጸዮን ገብረሚካኤል ስለአቶ ደበበ ምህረት ከሃላፊነት መነሳት " እሱም የሚመሰገነውን ያክል ጉድለትም እንደነበረበት ይረዳል። ከሃላፊነቱ ሲነሳም አልደነገጠም።" በማለት መናገራቸው ይታወቃል። ምንም እንኳ ዶ/ር ደብረጺዮን አቶ ደበበ በብቃት ችግር እንደተነሱ አድርገው ለመገናኛ ብዙሀን ቢገልጹም፣ አቶ ምህረት ደበበ ግን በህወሃት ባለስልጣናት ስውር እጅ ሲቀነባበር የነበረውንና ኢትዮጵያን ከ500 ሚሊዮን ብር በላይ እንድታጣ ያደረገውን ከፍተኛ ሙስና ሲቃወሙ እንደነበር ለጠቅላይ ሚ/ር ሃይለማርያም ደሳለኝ የቀረበው እና ለኢሳት የደረሰው የጸረ ሙስና ኮሚሽን የምርመራ ሪፖርት ያስረዳል።
በ1999 እና በ2000 ዓ.ም የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል ኮርፖሬሽን የኤሌክትሪክ ኃይልን ተደራሽ ለማድረግ የሚረዱ ትራንስፎርመሮችን ለመግዛት ካወጣቸው አለም አቀፍ ጨረታዎች ጋር ተያይዞ በጨረታዎቹ ሂደት ላይ ግልጽነትና ኃላፊነት የጎደለው አሰራር መከሰቱንና ይህም የኤሌክትሪክ ኃይልን ለማዳረስ በሚደረገው ጥረት ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ሊያሳርፍ እንደሚችል የፌደራል የሥነምግባር እና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ምርመራ በማድረግ የምርመራ ውጤቱን በወቅቱ በስልጣን ላይ ለነበሩት ለጠቅላይ ሚኒስትት መለስ ዜናዊ አቀረበ።

በአዲስ አበባ የቅርብ ጊዜ የጅምላ መቃብር ተገኘ

December 30, 2013
ሁኔ አቢሲኒያዊ
ነገሩ የተከሰተው አርብ እና ቅዳሜ እለት ነው ከስድት ኪሎ ወደ ፈረንሳይ በሚወስደው መንገድ ላይ በሚገኘው የጃንሜዳ ጦር ካምፕ(በቀድሞ ስሙ ሦስተኛ ሻለቃ) ግቢ ውስጥ በትንሹ ወደ 6 የሚጠጉ አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተገኝተዋል! አስከሬኖቹ ሊገኙ የቻሉት ለመንገድ ስራ የጦር ካምፑ ግቢ አጥር ወደ ውስጥ ፈርሶ መቆፈር ነበረበት፡፡ በዚህ ሂደት ላይ ነው እንግዲህ በስካቫተር ሲቆፈር በመጀመሪያ ሁለት አስከሬኖች በብርድልብስ እንደተጠቀለሉ ተንከባለሉ፡፡ በዚህ የተደናገጡት ሰራተኞች ለጊዜው ስራቸን ያቋረጡ ሲሆን በበነጋው ቅዳሜ እለት ረፋዱ ላይ በሌላ አቅጣጫ ቁፋሮ ሲያደርጉ በዛም በኩል እዲሁ በብርድ ልብስ የተጠቀለሉ አራት አስከሬኖች በተመሳሳይ ሁኔታ ከአፈሩ ዉስጥ ተገኙ፡፡A mass grave in Addis Ababa, Ethiopia
በዚህ መሃል ከጦር ካምፑ አካባቢ የተወሰኑ መኮንኖችና ከፍተኛ ማዕረግ(ጄነራሎች)በትከሻቸው ላይ ያለባቸው ሰዎች ወደ ቦታው በመምጣት ስራው እንዲቆም ትእዛዝ ያስተላለፉ ሲሆን በአካባቢው የነበረውንም ሰው ከቦታው አባረው በትነዋል፡፡ በስፋራው ተገኝተው ሁኔታውን ሲከታተሉ እና በስራው ላይም ተሳታፊ የነበሩ ለሰማያዊ ፓርቲ ቅርብ የነበሩ ሰዎች ፎቶ ለማንሳት ጥረት ቢያደርጉም በወታደሮቹ ተመናጭቀዉ ክልከላ ደርሶባቸዋል፡፡ እንደምንጮቻችን እና የምስል ማስረጃዎች ከሆነ አስከሬኖቹ የተጠቀለሉበት ብርድልብስ አንዳችም ሳይቀደድና ሳይበሰብስ ከነአዲስነቱ መገኘቱ ጅምላ ግድያው በቅርቡ የተፈፀመ ሊሆን እንደሚችል ከፍተኛ ጥርጣሬን አሳድሯል! በጉዳዩ ላይ ማጣራት ለማድረግ ሙከራ ያደረጉት የሰማያዊ ፓርቲ አባሎችንም ፊት እንደተነሳቸውና ለማናገርም ፈቃደኛ የሆነ ሰው አለማግኘታቸዉንም እንዳዉም ቦታውን ባስቸኳይ እንዲለቁ ከሀይለ ቃል ጋር መታዘዛቸውንም ጨምረውተናግረዋል፡፡

Battles rage in South Sudan as ceasefire hopes fade; Uganda interferes

SOUT1December 30, 2013, Juba (AFP) — South Sudanese rebels allied to ex-vice president Riek Machar sought to retake control of a key town Monday, the army said, as hopes faded that an upcoming ceasefire deadline will be obeyed in the violence-wracked nation.
United Nations peacekeepers said they were concerned over claims thousands of armed youths from Machar’s Nuer tribe were readying to attack Bor, the capital of Jonglei state, amid international efforts to stop two weeks of violence spiralling into all-out civil war.
“The forces of Riek Machar are now advancing on Bor, but we are confident we will hold them off and protect the town,” army spokesman Philip Aguer told AFP.
“Yesterday there were heavy clashes at Gadiang north of Bor… the people in Bor are fearing an attack at any time.”
Rebels were currently reported around 50 kilometres (30 miles) northeast of Bor.
It was not clear how many of the gunmen remained in the thick bush around Bor, but the army statement appeared to contradict claims by government spokesman Michael Makuei late on Sunday that “most of them have returned home”.
Reconnaissance flights by the UN Mission in South Sudan (UNMISS) on Sunday identified armed groups but could not confirm the force’s size.
The gunmen, a loose ethnic militia force loyal to Machar and dubbed the “White Army”, are heavily armed — some carrying automatic rifles or spears, others armed with rocket propelled grenades. They are known for smearing white ash onto their bodies as war-paint and to ward off insects.
The world’s youngest nation plunged into chaos on December 15 when President Salva Kiir accused his former deputy of mounting a coup, sparking deadly violence believed to have left thousands dead.
Ceasefire deadline Tuesday
Regional leaders at the Inter-Governmental Authority on Development (IGAD) have set Tuesday as a deadline for face-to-face talks between Kiir and Machar.
While the government has said it was willing to observe a ceasefire, Machar — who was sacked as vice-president in July — has made demands including the release of his arrested political allies before committing to a truce.
South Sudanese government spokesman Makuei told AFP on Sunday: “I really doubt if we, the South Sudanese government, will be in a position to sit with Riek Machar… He has not even respected the call by IGAD and the African Union to agree to the cessation of hostilities.”
Fuelled by ethnic rivalries between Kiir’s Dinka group and Machar’s Nuer, bloodshed has swept across the nation, with fierce battles reported in strategic oil-producing areas.
Grim reports of massacres, rapes and killings nationwide have emerged on both sides of the conflict.
Rebels swiftly took over several key regional cities including Bentiu, in the northern oil-producing state of Unity, and Bor, which was later recaptured by the army.
There was also heavy fighting in the town of Malakal, state capital of oil-producing Upper Nile, but the army said they were back in full control.
A video posted by UN humanitarian chief in South Sudan Toby Lanzer in Malakal showed burnt and looted stores and buildings in the centre of town.
“The situation in Malakal is stable, we are in control,” Aguer added.
Oil production, which accounts for more than 95 percent of South Sudan’s fledgling economy, has also been hit with oil companies evacuating employees.
The UN says some 75,000 have sought refuge in badly overstretched peacekeeper bases across the country, and over 180,000 are displaced across the country.
Tens of thousands of Sudanese refugees are also reported to have been affected.
UN peacekeeping reinforcements began arriving in the country last week, the spearhead force of some 6,000 extra troops voted for by the UN Security Council, that will nearly double the size of the mission in the country.
UNMISS chief Hilde Johnson is to brief the UN Security Council later Monday on the crisis.
South Sudan became independent in 2011 after a civil war that killed more than two million people between 1983 and 2005.
Source: AFP

December 30, 2013, JUBA, South Sudan (AP) — An official says Ugandan President Yoweri Museveni is in South Sudan to advance regional efforts to find a political solution to the country’s crisis.
Fred Opolot, a spokesman for Uganda’s Foreign Ministry, said Monday that Museveni visited South Sudan “in the spirit” of diplomatic efforts by East African leaders who want President Salva Kiir and his rivals to start peace talks by Tuesday.
Museveni, a strong ally of Kiir’s, has deployed troops to Juba, the South Sudan capital, but the military denies Uganda has taken sides in the conflict.
Ugandan military spokesman Lt. Col. Paddy Ankunda said Ugandan forces were stationed at the airport and their role is to “facilitate evacuation” of civilians.
Up to 180,000 people have been displaced by violence since Dec. 15, according to the U.N.
Source: AP

Sunday, December 29, 2013

ፓትርያሪክ አቡነ መርቆሬዎስ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በጽሁፍ ማብራሪያ አወጡ


 “ህመምና ስደት የተባበሩበት ሰው በመጠኑም ቢሆን ማሰቡ አይቀርም ሆኖም ግን እግዚአብሔር ሰው ሲሰጥ ደግሞ ኅዘንም መከራም ይረሳል።” ከ4ኛው ፓትርያሪክ አቡነ መርቆርዮስ በወቅታዊ ጉዳዮች ዙሪያ ካወጡት ወቅታዊ ጽሁፍ የተቀነጨበ።

በሰሜን ሸዋ ዞን ሞተዋል ተብለው ፍታት ሲደረግላቸው የነበሩት አዛውንት ከሞት ነቁ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2006 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሲያ ደብር ዋዩ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የ65 አመቱ አዛውንት አቶ ሃይሉ በልሁ ከቀናት ህመም በኋላ ታህሳስ 16 ቀን 2006 ዓ.ም ህይወታቸው አልፏል ። የቅርብ ወዳጅ ዘመድ እስኪሰበሰብ ድረስም ቀብራቸው እንዲዘገይ ይደረጋል።
በአካባቢው ባህል መሰረትም ከ18 ሰዓታት ቆይታ በኋላ በባህሉ መሰረት የቤተክርስቲያን ካህናት ተገኝተው ፍታት ያደርጉላቸዋል፥ ይሁን እንጅ በዚህ ጊዜ ያልተለመደ እና እንግዳ ነገር ይከሰታል። ይኸውም ካህናቱ የሟች አስክሬን ባለበት ሳጥን ውስጥ የሰው ድምጽ እንደሰሙ በመናገር ሳጥኑ ይከፈት ዘንድ ያዛሉ።
ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይም ሞተዋል የተባሉት አዛውንት ያሉበት ሳጥን እንዲከፈት ሲደረግ፥ አቶ ሃይሉ በህይዎት ነበሩ ። ህይዎታቸው አልፏል ተብለው ለቀብር የተዘጋጁት አቶ ሃይሉ ግንዛቱን ፍቱልኝ በማለትም የሚጠጡት ውሃ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
ለለቅሶ የተሰበሰበው ቤተ ዘመድም በውሃ ፈንታ አጥሚት በማዘጋጀት ከሰጧቸው በኋላ አቶ ሃይሉ ደህና መሆን ችለዋል። አዛውንቱን ለመቅበር የተሰበሰበው ዘመድ አዝማድም በደስታ ተለያይቷል።
መረጃውን የሲያ ደብር ዋዩ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አድርሶናል።

Ethiopia’s New Plan to Hunt, Kill or Maim Ogaden citizenry in the Diaspora

Ogaden_Map1December 29, 2013 (Ogaden Online) — The Ogaden Online News Network’s investigators have received confidential  information about a new clandestine plan to hunt, kill, maim, or intimidate, at the very least, the Ogaden citizenry in the Diaspora  especially in the Kenyan refugee camps and those present in the Kenyan capital, Nairobi.
This plan is spearheaded by the Ethiopian Intelligence using the Ethiopian military personnel at the Moyale, Kenya border, the Ethiopian embassy in Nairobi and members of its Kilil personnel both in Kenya and in JigJiga.
What the Ethiopian intelligence has done over the past one year is to collect the names, family history and even the pictures of the Ogaden leaders at the Kenyan refugee camps. They have also obtained, from those who have defected in the past six months, the same information concerning the leaders of the Ogaden citizenry living in the Kenyan capital.

የጋዜጠኞችና የጋዜጠኝነት ይዞታ በኢትዮጵያ

በአሁኑ መንግሥት ሳንሱር ሲነሳ የግል ጋዜጦች ቁጥር ከፍ ቢልም በሂደት ግን ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ቀርተዋል ፤ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የጋዜጠኞች መከሰስ መታሰርና ከሀገር መሰደድ ተባብሷል ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሱት የሃገሪቱ የፕሬስና የፀረ ሽብር ሕግ ናቸው ።
በኢትዮጵያ ጋዜጠኝነት በየስርዓቱ ባጋጠሙት ልዩ ልዩ እንቅፋቶች ሰበብ የሚጠበቅበትን ሚና መጫውት እንዳልቸለ የመስኩ ባለሞያዎች ያስረዳሉ ። ባለሞያዎች እንደሚሉት ለዚህ አብዩ ምክንያት ሙያው በተለይ በየስርዓቱ የሚደርስበት ፖለቲካዊ ጫና ነው ። በኢትዮጵያ በቀደሙት ሁለት መንግሥታት መገናኛ ብዙኃን በሳንሱር ማነቆ ስር ነበር የሚሰሩት። በአሁኑ መንግሥት ሳንሱር ሲነሳ የግል ጋዜጦች ቁጥር ከፍ ቢልም በሂደት ግን ቁጥራቸው አሽቆልቁሎ አሁን በጣት የሚቆጠሩ ብቻ ቀርተዋል ፤ ከ1997 ምርጫ ወዲህ የጋዜጠኞች መከሰስ መታሰርና ከሃገር መሰደድ ተባብሷል ። ለዚህም በምክንያትነት የሚነሱት የሃገሪቱ የፕሬስና የቨረ ሽብር ሕግ ናቸው ። የጋዜጠኞችና ሰነ ምግባር እና የሙያ ብቃት ጉድለትም በሀገሪቱ ጋዜኝነት ተገቢውን ድርሻ ላለመወጣቱ በምክንያትነት ይጠቀሳሉ ። እንወያይ በኢትዮጵያ የጋዜጠኞችና የጋዜጠኝነትን ይዞታ ይቃኛል ። ተወያዮቹ የሬፖርተር ጋዜጣ አዘጋጅ የማነ ናግሽና የቀድሞው የአዲስ ነገር ጋዜጣ አዘጋጅ መስፍን ነጋሽ ናቸው ።
ኂሩት መለሰ
ማንተጋፍቶት ስለሺ

AUDIOS AND VIDEOS ON THE TOPIC

  • ቀን 29.12.2013

ሰበር ዜና፣ በዓረና-ትግራይ ስብሰባ መታወቅያ የሌለው እንዳይገባ ተከለከለ

Tigray, Ethiopia mapDecember 29, 2013
by Abraha Desta
በሽሬ እንዳስላሴ ከተማ እንገኛለን። የህዝብ ስብሰባው ለመጀመር አዳርሹ ሲከፈት ህዝብ በስብሰባው ለመሳተፍ መግባት ሲጀምር አስተዳዳሪዎቹ ደንግጠው ‘በስብሰባው መሳተፍ የሚችል ሰው የቀበሌ መታወቅያ ያለው’ ብቻ መሆን እንዳለበት አወጁ። መታወቅያው እየመዘገቡ ለማስገባት ወሰኑ። ህዝቡ ተቃወመ። የዓረና አመራር አባላትም ድርጊቱ ተቃወሙ። መታወቅያ የሌለው እንዳይገባ ስለተወሰነ ብዙ ሰው ተቃውሞ ስላነሳና መግባት ስለፈለገ የአዳራሹ መግብያ በር ተዘጋ። አሁን የተፈቀደልን አዳራሽ ዝግ ነው። ዓረና ስብሰባው በአዳራሹ በር ባለው ሜዳ ለማካሄድ ወስኗል። ባደራሹ በር አከባቢ ብዙ ህዝብ አለ። ካድሬዎቹ ህዝቡ ለመበተን እየፈተኑ ነው።

Abune Mathias arrested and released

Abune Mathias arrested and released
Ethiopian Review:-The TPLF-installed illegal patriarch in Ethiopia, Abune Mathias, has been temporarily placed under arrest and was released after being interrogated for 72 hours by Tsegaye Berhe, National Security Adviser to the Prime Minister, and other security officials, according to Ethiopian Review sources in Addis Ababa.Leaders of the TPLF junta are apparently upset with statements that have been uttered by Abune Mathias over the past 3 weeks that were critical of the tribal regime. In one particular meeting, Abune Mathias was heard saying that much of the problems facing the church are caused by the ruling party.The Ethiopian Orthodox Church’s
administration in Addis Ababa is currently paralyzed by a growing leadership crisis. Many church leaders are in open revolt and have refused to take orders from the Holy Synod.

Ethiopian maid found hanging in South Lebanon

Ethiopian maid found hanging in South Lebanon
Al-Akhbar:- An Ethiopian woman was found hanging from an electrical cord outside her employer’s South Lebanon home in an apparent suicide, state news reported Saturday.
The National News Agency identified the victim as Dimi Kash-Kalashou Kata. It published a disturbing image of the woman hanging by her neck in the southern town of Rmeich.
Police have launched an investigation into the incident, the report said, adding that they believed the woman hung herself as is common among maids in Lebanon, which hosts about 200,000 domestic workers.
Domestic workers in Lebanon and other Arab countries are employed under the heavily criticized sponsorship, or kafala system which denies the maid the right to terminate her contract or leave her employer.
Maids employed under this system are not covered by Lebanese labor laws, meaning they have no minimum wage, social security or other basic rights.
It is almost always the case that an employer holds the maid’s passport over fears she might run away. It is also common for an employer to lock the maid inside their home when they leave the house or travel.
In July a Bangladeshi worker was found hanging in her employer’s home in East Lebanon, and a month before that a pregnant Ethiopian maid committed suicide in Mount Lebanon.
Human Rights Watch documented an average death rate of one per week among domestic workers due to unnatural causes in 2008. Those cases included suicides and death by falling from buildings.
via:http://www.harartubes.com

Ethiopians returning from Saudi Arabia face uncertainty in their homeland

More than 135,000 Ethiopians have been deported from Saudi Arabia as illegal and undocumented workers. The returnees include many women who are unsure about what future awaits them in Ethiopia. Marthe van der Wolf reports for VOA from Addis Ababa.

በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው የግንቦት የታጠቀ ቡድን በሰነይ በረሃ በኤርትራ ውስጥ የሚያደርገው እንቅስቃሴ በመክሸፉንና ታጣቂዎቹ ወደ ሱዳን የፖለቲካ ጥገኝነት እንደጠየቁ ተዘገበ።

ERITREA/GINBOT 7 Via#Girum Zeleke#
በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ የሚመራው የግንቦት የታጠቀ ቡድን በሰነይ በረሃ በኤርትራ ውስጥ የሚያደርገው እንቅስቃሴ ሙሉ ለሙሉ በመክሸፉንና ታጣቂዎቹ ወደ ሱዳን የፖለቲካ ጥገኝነት እንደጠየቁ ተዘገበ። ግንቦት ህዝባዊ ሃይል በአሁኑ ወቅት ከ20 እስከ 30 የሚደርሱ የሰራዊት አባላት ብቻ እንዳሉት ይህ የታመነው የዜና ምንጭ አስታውቋል።

ከሁለት ወር በፊት በፃፍኩት ተመሳሳይ ዘገባ በአደረጃጀት ችግር ምክንያት ከ120 በላይ የያዘ ህዝባዊ ሃይል ለማዋቀር አለመቻሉን በትንታኔ አቅርቤ ነገር ግን በቅርብ የማውቃቸው የድርጅቱ ደጋፊዎች በተለያዮ አልባሌ አነጋገሮች ዘገባውን የወያኔ ወሬ ነው ብለው አጣጥለውት እንደነበር ይታወሳል። የዜናው ምንጭ ከአለም ዲፕሎማቲክና ስለላ ማህበረሰብ ጋር የጠበቀ ግንኙነት ያለው The Indian Ocean Newsletter የአፍሪካ ኢንተለጀንስ ዜና አውታር ነው።

በ መስከረም 02/2013 የታላቋ ብሪታንያ የመከላከያ ሚኒስትር የበላይ አማካሪ የሊብራል ዲሞክራቱ ኒክ ሃርቬይ ከወያኔ የውጭ ጉዳይ ልኡካን ጋር ባደረጉት ቃል ምልልስ በኤርትራ አለ የተባለውን ወታደራዊ እንቅስቃሴ እንደማያምኑበት ከታላቋ የብሪታንያ አለም አቀፍ ወታደራዊ ኢንተለጀንስ ቢሮ ባላቸው መረጃ ማወቅ መቻላቸውን አስረድተዋል።

ይህ እንዲህ እንዳለ ከዚህ በፊት ከድርጅቱ አመራር የአነጋገር ዘይቤዎች ሳይቀር ህዝባዊ ሃይል የማደራጀቱ ስራ ምንም ያክል እንዳልተራመደ የሚጠቁሙ መሆናቸው ግልፅ ነው። በመስከረም 28/2013 ኦስሎ ከተማ ከተደረገው የግንቦት 7 ሕዝባዊ ግንባር ገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅት በኋላ የግንቦት 7 ምክትል ሊቀመንበር አቶ አንዳርጋቸው ፅጌ October 1, 2013 ለ ESAT በሰጡት መግለጫ በሕዝባዊ ግንባሩ ስም ከዚያን ቀን በኋላ ምንም አይነት የገንዘብ ማሰባሰቢያ ዝግጅቶች እንዳይካሄዱ ማዘዛቸው ሊዋቀር የታሰበው ሠራዊት ካለመኖሩ ጋር ተያይዞ ከጊዜ በኋላ ከሚመጣው ተጠያቂነት ለመዳን መሆኑ ግልፅ ነው።
"Andargachew Tsige, the Secretary General of the opposition Ginbot 7 Movement said that they are forming their own network within the Ethiopian Defense Forces. He said this after a successful fund raising event held in Norway over the weekend." .... "He also stressed that there should not be any fund raising event in the name of the Popular Force or individuals until the Force makes its own fund raising programs public in the future."

Source: http://ethsat.com/2013/10/02/g7-is-forming-a-network-within-the-defense-forces-andargachew/

The Indian Ocean Newsletter Dated 28/09/2013

Saturday, December 28, 2013

ኸርማን ኮኸን ምን ይፈልጋሉ?

‹‹እኝህ ሰውዬ የሁለቱን አገሮች ዕርቅ ለማሳካት ሞራላዊ ብቃት የላቸውም፡፡ እንደ ኢትዮጵያዊ ሳስበው ደም መለገስ እንጂ ከኤርትራ የምናተርፈው   ምንም ነገር የለም፡፡
ኤርትራ መቼም ሰላማዊ ጎረቤት መሆን አትችልም፡፡ ቅኝ ገዥዎችና የሁለቱ አገሮች መሪዎች ታሪክን ንደዋል፡፡ ያንን ለማስተካከል ሌላ ምዕተ ዓመት ይፈጃል፡፡ ለተረጋጋች ኢትዮጵያ ኤርትራ ባለችበት መደንዘዝዋ ጥሩ ዕድል ነው፡፡  የኢትዮጵያ መንግሥት ከኤርትራ ጋር ዕርቅ በመፈጸም ዳግም ታሪካዊ ስህተት  እንዲፈጽም ዕድል መሰጠት የለበትም፡፡ አሁንም ውስጥ ያሉት አልተውንም፡፡ ለራሱ ለመንግሥትም አደጋ ናቸው፡፡ መጠንቀቅን ቢረዳ መልካም ነው፡፡ የሻዕቢያ የስለላ መዋቅር አደጋ ነው፡፡ ያን አደጋ መከላከል የሚቻለው አሁን ባለን የባላንጣነት ጉርብትና ሒደት ውስጥ ነው፡፡››
ይኼ አስተያየት በሪፖርተር ድረ ገጽ  ከተሰጡት በርካታ ተመሳሳይ አስተያየቶች መካከል አንዱ ሲሆን፣ በአሜሪካ ስቴት ዲፓርትመንት የአፍሪካ ጉዳዮች ረዳት ሚኒስትር የነበሩት ኸርማን ሐንክ ኮኸን፣ ኢትዮጵያንና ኤርትራን ለማስታረቅ ‹‹ጊዜው አሁን ነው›› በሚል ለተመድ ያቀረቡት የመፍትሔ ሐሳብ ከተዘገበ በኋላ የወጣ ነው፡፡

ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ የተባሉት የፌዴራል ፖሊስ አባል ቅጣት ተወሰነባቸው

-ለ30 ዓመታት ማገልገላቸውን ተናገሩ
የወንጀል ሕግ አንቀጽ 449(1)ሀን በመተላለፍ የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ዳኛን በማመነጫጨቅ፣ የፍርድ ቤትን ክብር በመንካትና ፍርድ ቤት በመድፈር ወንጀል ጥፋተኛ ተብለው የነበሩት የፌዴራል ፖሊስ አባል ኢንስፔክተር ሙሉ አሰፋ፣ በስድስት ወራት ቀላል እስራት እንዲቀጡ ታኅሣሥ 17 ቀን 2006 ዓ.ም. ውሳኔ ተላለፈባቸው፡፡ 
የቤተሰብ ኃላፊ መሆናቸውንና ላለፉት 30 ዓመታት ከበረሃ ጀምሮ በውትድርና ዓለም ተሰማርተው በነበሩበት ወቅት፣ አንድም የወንጀል ድርጊት ፈጽመው እንደማያውቁ፣ የቅጣት ውሳኔውን ላስተላለፈባቸው የፌዴራል የመጀመሪያ ደረጃ ፍርድ ቤት ልደታ ምድብ ሁለተኛ ፍትሐ ብሔር የቤተሰብ ችሎት ያስረዱት ኢንስፔክተር ሙሉ፣ በወቅቱ (ታኅሣሥ 11 ቀን 2006 ዓ.ም.) ከሥራ ጋር በተያያዘ ተበሳጭተው በነበሩበት ወቅት ችሎቱን መረበሻቸውን አምነዋል፡፡
‹‹ለችሎቱ መታዘዝና ክብሩንም መጠበቅ ነበረብኝ፡፡ ይኼንን ባለማድረጌ ጥፋተኛ ነኝ፤ ተፀፅቻለሁ፡፡ ይቅርታ ይደረግልኝ፤›› በማለት ችሎቱን ተማፅነው ነበር፡፡ 
ፍርድ ቤቱ ጥፋተኛ መሆናቸውን ብይን የሰጠበት የወንጀል ሕግ 449(1)ሀ፣ ከአንድ ዓመት ባልበለጠ ቀላል እስራት ወይም ከ3,000 ብር ባልበለጠ የገንዘብ ቅጣት የደነገገ በመሆኑ፣ ኢንስፔክተር ሙሉ ጥፋተኛ ለተሰኙበት ፍርድ ቤት የመድፈር ወንጀል ድርጊት፣ በተፈጸመው የወንጀል ድርጊት ላይ ብይን ከተሰጠ በኋላ የሚያዋጣው ጥፋትን አምኖ [ተፀፅቻለሁና ይቅርታ ይደረግልኝ ሳይሆን ተገቢ የሆነ የቅጣት ማቅለያ ማቅረብ ነው]  በሚል የቅጣት ማቅለያ ሐሳብ እንዲያቀርቡ ፍርድ ቤቱ አዟል፡፡

የ5 ዓመት ህፃን ከት/ቤት ፎቅ ወድቃ ሞተች

አራት የት/ቤቱ ሰራተኞች ከስራ ታግደዋል:: የምሥራቅ ጮራ መዋለ ህፃናትና አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመዋዕለ ህፃናት ተማሪ የነበረችው የ5 ዓመቷ ህፃን ሳባህ አማን ከት/ቤቱ 3ኛ ፎቅ ላይ ወድቃ፣ በጥቁር አንበሳ ሆስፒታል በህክምና ስትረዳ ቆይታ በአራተኛ ቀኗ ባለፈው እሁድ ህይወቷ አልፏል፡፡ ጉሊት በመነገድ ከሚተዳደሩ አክስቷና ከ12ኛ ክፍል ተማሪ እህቷ ጋር ትኖር የነበረችው ሕፃን በአሁኑ ዓመት ነበር ትምህርት ቤት የገባችው፡፡ ለብቻው ከተከለለው መዋዕለ ህፃናት እንዴት ወደ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ገብታ፣ ከፎቅ ላይ እንደወደቀች እንደማያውቁ የተናገሩት ቤተሰቦች፤ ህፃኗን ስትወድቅ ማንም እንዳልነበረና የትምህርት ቤቱ የካፍቴሪያ ሰራተኛ መሬት ላይ ወድቃ እንዳገኛት ጠቁመዋል፡፡ ልጅቷ ስትወድቅ እንዴት አስተማሪዎች ወይም ሞግዚቶች እንዳላዩ ት/ቤቱን መጠየቃቸውን የገለፁት ቤተሰቦች፤ ከት/ቤቱ “ስብስባ ላይ ነበርን” የሚል ምላሽ ማግኘታቸውን ተናግረዋል፡፡ የምስራቅ ጮራ ት/ቤት ርእሰ መምሕር አቶ ስንታየሁ አንሺሱ ስለ አደጋው ሲናገሩ፤ “ሳምንታዊ ስብሰባ የምናደርግበት ቀን ስለነበር አጠቃላይ የት/ቤቱ መምህራንና ሰራተኞች ተሰብስበን ሳለ ከቀኑ 9፡40 ላይ አንዲት ተማሪ ከፎቅ ወድቃለች ተባልን።

“ካልተሳፈርኩ” ብሎ የታክሲ ሹፌሩን በሽጉጥ ገደለ

መገናኛ አካባቢ ወደ ጉርድ ሾላ በሚወስደው መስመር፣ አንድ መንገደኛ ትናንት ከምሽቱ 12 ሰዓት ላይ ሚኒባስ ታክሲ ውስጥ ካልተሳፈርኩ ብሎ ሾፌሩን ወንደሰን ደምሴን በሽጉጥ ገደለ፡፡ “ታክሲው ውስጥ ካልተሳፈርኩ፣ አትሳፈርም” በሚል በተነሳው ጭቅጭቅ፣ ሾፌሩን ገድሏል የተባለውን ደጀኔ ገመቹ በቁጥጥር ስር እንደዋለ የገለፀው ፖሊስ፤ የአይን ምስክሮችን ቃል በመቀበል ምርመራ እያካሄደ ነው፡፡ ታክሲ እየጠበቁ የነበሩ የአይን ምስክሮች በወቅቱ አቶ ደጀኔ እጁን በማወዛወዝ ሚኒባስ ታክሲውን እንዳስቆመ ተናግረው፣ ከሾፌሩ ጋር ጭቅጭቅ እንደተፈጠረ ገልፀዋል፡፡ አቶ ደጀኔ በታክሲው ለመሳፈር ሲጠይቅ፣ ሾፌሩ “ቤተሰቤን ነው የጫንኩት፣ ሌላ ሰው አላስገባም” በማለት ምላሽ እንደሰጠው በአካባቢው የነበሩ መንገደኞች ተናግረዋል፡፡ ታክሲ የሚጠባበቁ ብዙ ሰዎች በአካባቢው ስለነበሩ፣ ጭቅጭቁን ከመነሻው እስከ መጨረሻው የተመለከቱ እማኞች በርካታ ናቸው፡፡ የፖሊስ መረጃ እንደሚጠቁመው፤ የሾፌሩ አባት ታክሲው ውስጥ ነበሩ፡፡ “አትሳፈርም የምትለኝ ንቀት ነው” በሚል ክርክርና “የጫንኩት ቤተሰቦቼን ስለሆነ ሌላ ሰው አልጭንም” በሚል ምላሽ በተባባሰው ጭቅጭቅ፣ አቶ ደጀኔ ሽጉጥ እንዳወጣ እማኞች ተናግረዋል፡፡ ሽጉጡን ሾፌሩ አንገት ስር በመደገን ነው የተኮሰው ብለዋል-ምስክሮች፡፡ በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የሰው መግደል ዲቪዥን ክፍል ተወካይ፣ ተጠርጣሪውን በቁጥጥር ስር በማዋል ምርመራ እየተካሄደ መሆኑን ገልፀዋል።
via:addisadmassnews.com

Friday, December 27, 2013

በጎንደር ዳባት ሕጻን ሰለሞን ላይ ማን የጥይት እሩምታ አወረደበት?

ከዳዊት ሰለሞን
ሰሜን ጎንደር ዳባት ወረዳ ነዋሪ የነበሩት የ55 ዓመቱ አቶ ማስረሻ ጥላሁን የተመሰከረላቸው አርሶ አደር ገበሬ በመሆናቸው የክልሉ ግብርና ጽ/ቤት ሞዴል አርሶ አደር በማለት ሸልሟቸዋል፡፡የሁለት ወንድና የአምስት ሴት ልጆች አባት የሆኑት አቶ ማስረሻ ወሰኔን ገፍተሃል የሚል ክስ ቀርቦባቸው በዳባት ፍርድ ቤት 300 ብር መቀጮ ተጥሎባቸው በመክፈል ወደ እርሻቸው ቢመለሱም የገበሬ ቀበሌ ማህበሩ ሊያስቀምጣቸው አልቻለም፡፡
ጥቅምት 15/2006ዓ.ም ከሁለተኛ ልጃቸው ሰለሞን ማስረሻ ጋር አትክልት ተክለው አመሻሹ ለይ ተዳክመው መኖሪያ ቤታቸው ገብተዋል፡፡ማለዳ 12፡00 ከመኝታው ባላቋረጠው የውሾች ጩህት ከእንቅልፉ ተነሳው ሰለሞን በሩን ከፍቶ ሲወጣ የጥይት እሩምታ ይወርድበታል፡፡አባት ልጄን ብለው የሌሊት ልብሳቸውን እንደለበሱ ወደ ውጪ ሲወጡ የጥይቶቹ አቅጣጫ ወደ እርሳቸው በመዞሩ ማን እንደተኮሰባቸውና ማን እንደመታቸው ለማየት እንኳን ሳይታደሉ ይህችን ጨካኝ አለም ተሰናበቱ፡፡
መኖሪያ ቤቱ ላይ በሚወርደው የጥይት እሩምታ የተነሳ ሁለት ላሞችና አንዲት ጊደር ተገደሉ፡፡የስምንት አመቷ ስለእናት ማስረሻ ቀኝ እጇ ላይ በጥይት ተመታች፡፡ባለቤታቸውን በሞት የተነጠቁትና ምንም የማታውቀውን ህጻን ልጃቸውን አካለ ጎደሎ ያደረገባቸውን ጥይት ማን እንደተኮሰው ለማወቅ ለዳባት ወረዳ ፖሊስ ጣቢያ አቤት ሲሉ ‹‹ባለቤትዎ ሽፍታ መረጃ ስለደረሰን ግድያውን የፈጸመው የጸረ ሽብር ግብር ሃይል ነው››ተብለዋል፡፡‹‹ሽፍታ እንዴት ባለ80 ቆርቆሮ ቤት ይሰራል?ልጆቹን ያስተምራል?ሞዴል አርሶ አደር ተብሎ ይሸለለማል?በየት አገር በብአዴን ስብሰባ ላይ እንድትገኝ ተብሎ በደብዳቤ ይጠራል?እንዴት ሽፍታ የመለስ ዜናዊን አደራ ለመወጣት በምንችልበት ሁኔታ ለመወያያት እንድንነጋገር ይባላል? ›› ጥያቄዎቹን ፖሊሶቹ ሊመልሱላቸው ባለመቻላቸው ወደ ክልሉ አስተዳደር አምርተዋል፡፡ክልሉ ለዞኑ ዞኑ ለወረዳው ደብዳቤ እየጻፈ እስካሁን ድረስ የአቶ ማስረሻ እውነተኛ የግድያ መንስኤ መታወቅ አልቻለም፡፡

South Sudan Agrees to Ceasefire to End Violence – Ethiopia and Kenya support Kiir

December 27, 2013, Nairobi (All Africa) — South Sudan’s government on Friday has agreed to a ceasefire in a bid to end fighting that swept across Africa’s newest nation that has left at least 1,000 people dead and led more than 60,000 civilians to seek refuge at U.N. bases.
A spokesman for South Sudan’s foreign ministry, Mawien Makol Arik told VOA the government’s ceasefire will begin immediately. Arik says Vice President Riek Machar, the leader of the rebellion, has three days to respond to the ceasefire call.
The development came as regional leaders meeting in the Kenyan capital, Nairobi, Friday as part of the regional grouping IGAD urged both sides in the conflict to seize “the small window of opportunity” and begin peace talks.
At the same time the leaders said they would not accept the “unconstitutional overthrow” of South Sudan’s government.

Freedom is never given voluntarily, it has always been earned

By Ibrahim Amae Elemo, M.D., M.P.H | December 27, 2013
Dear Friends and Colleagues, Obboleeyyan Oromoo akkam jirtu, nageennii isan badhaadhaa:
The bigotry against the Oromo people continues unabated to date. It is an established historical fact that the Oromo people, the Somali and other peoples of the South were conquered and incorporated into the Abyssinian Empire at the end of 19th century through an earth scorching policy and savagery of Menelik’s army supported by western powers such as the Great Britain and France. Twenty years ago we were close to defeating the remnants of the genocidal regime of Menelik and Haile Selassie had it not been for the voice of moderation by some politicians in the Oromo Liberation camp. Back then some of the Oromo elites wanted to give peace a chance, wanted to negotiate with the colonial settlers. They chose the path of peace and reconciliation. We recall the famous saying of Leenco Lata, “I am not an Ethiopian. However, I would like to negotiate to be an Ethiopian”. The answer to that offer from these remnants twenty years later is the formation of the revivalist groups who are planning to tour Oromiya to dance on the graves of the millions of Oromo martyrs and other peoples of the South who were brutally massacred while defending their homeland. The aftermath of the conquest was what we now know as one of the worst slave trade empire built by Menelik. I can hardly imagine the extent of the brutality when hundreds of thousands of Oromo children were taken way from under the arms of their loving parents and sold into slavery; tragically, several of whom died en route owing to harsh conditions. These were a people, reduced in to slavery and tenancy, were once the master of their own destiny and produced to the world a civilization superior to the Abyssinian civilization in East Africa.  This is also an established historical fact.

የጁነዲን ባለቤት ወ/ሮ ሃቢባ መሐመድ በድርድር እንደተፈቱ ታውቋል::

አባዱላ ገመዳ እንዲሁም ደ/ፂዮንና ፀጋዬ በርሄ ከጁነዲን ጋር ተደራድረዋል::
የቀድሞ የኦህዴድ/ኢህአዴግ አመራር አባልና ሚኒስትር የነበሩት አቶ ጁነዲን ሳዶ ባለቤት በውስጥ በተደረገ ድርድር ከእስር እንዲለቀቁ መደረጉን የቅርብ ምንጮች ለዝግጅት ክፍላችን ገለጹ።

« ከሳኡዲ ኤንባሲ ገንዘብ ተቀብለው ሲወጡ እጅ ከፍንጅ ተይዘዋል» በሚል በሽብርተኝነት ወንጀል እንዲከሰሱ የተደረጉትና ለአንድ አመት የታሰሩት የአቶ ጁነዲን ባለቤት ወ/ሮ ሃቢባ መሐመድ ከሕወሐት መሪዎች በተላለፈ ቀጭን ትእዛዝ እንዲፈቱ መደረጉን የጠቆሙት ምንጮቹ አክለውም ይህ ሊሆን የቻለው በስደት ከሚገኙት አቶ ጁነዲን ሳዶ ጋር በተደረገ ምስጢራዊ ድርድር ላይ “መንግስት ከዚህ ቀደም በወሰዳቸው እርምጃዎች፣ ፖለቲካዊ ምስጢራዊ ጉዳዮችና ገዢውን ፓርቲ የሚመለከቱ ማንኛውም ነገሮች በየትኛውም ቦታ ላለማጋለጥ፣ ላለመናገር፣..” ከጁነዲን ጋር ከስምምነት ከደረሱ በኋላ ባለቤታቸው እንዲፈቱ መደረጉን አስታውቀዋል።

በሙስና የተጨማለቁት አባዱላ ገመዳ እንዲሁም ደ/ፂዮንና ፀጋዬ በርሄ ከጁነዲን ጋር እንደተደራደሩ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል። መጀመሪያም ወ/ሮ ሃቢባ የሰሩት ወንጀል ኖሮ አይደለም የታሰሩት ያሉት ምንጮቹ አቶ ጁነዲን ከስልጣን ለማንሳት ሲባል ብቻ የተወሰደ እርምጃ መሆኑን ገልፀዋል። ጁነዲን ባለቤታቸው ከታሰሩ በኋላ በስልጣን ላይ እያሉ እንዲያውም ያለመከሰስ መብታቸው ሳይነሳ ሚሚ ስብሃቱ በምታዘጋጀው ራዲዮ ጣቢያ « ጁነዲን መታሰር አለባቸው፤ መንግስት እስከ አሁን እርምጃ የማይወስደው ለምንድነው?..ባለቤታቸው አሸባሪ ናት» በማለት የፍ/ቤትን ነፃነት ጭምር በሚጋፋ መልኩ ቅስቀሳ ይካሄድ እንደነበረ ምንጮቹ አስታውሰዋል። አቶ ጁነዲን ከአገር ከወጡ በኋላ እውነቱን እያወቁ መደራደራቸውና ባለቤታቸውን በማስፈታት ሌሎች ንጹሃን የሙስሊሙ ማህበረሰብ ተወካዮች ላይ በተዘዋዋሪ በመፍረድ የኢህአዴግና ካንጋሮው ፍ/ቤት ተባባሪ መሆናቸው አሳዛኝ ነው ብለዋል ምንጮቹ። አቶ ጁነዲን ምናልባትም « ባለቤቴ በፍ/ቤት ነፃ ተባለች» በሚል በኢትዮጲያ የፍትህና የፍ/ቤት ነፃነት እንዳለ አስመስለው ሊናገሩ እንደሚችሉ ማረጋገጫ የለም ያሉት ምንጮቹ አክለውም ጁነዲን ምንም አሉ ምን በስልጣን እያሉ ለፈፀሙት ወንጀል መጠየቃቸው እንደማይቀር መታወቅ አለበት ብለዋል።
Harartube//ከኢየሩሳሌም አርአያ/

Wednesday, December 25, 2013

በስዊድን ቅድስት ሥላሴ ቤተክርስቲያን ላልተወሰነ ጊዜ ተዘጋ

(ዘ-ሐበሻ) “ባለፉት ወራት በቤተክርስቲያናችን ውስጥ ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች በመከሰታቸውና ያለመግባባት በመፈጠሩ፤ ይህን ተከትሎ በማህበረ ምህመናኑ (አባቶች፣ እናቶች፣ ወንድሞች፣ እህቶችና ህፃናት ላይ ሊደርስ የሚችለውን አደጋ ግምት ውስጥ በማስገባት ከነገ ታህሳስ 13 ቀን 2013 (December 21,2013) ጀምሮ መንፈሳዊ አገልግሎቱን ለጊዜው እንድናቋርጥ ተገደናል” ይላል በስዊድን ስቶክሆልም ከተማ ውስጥ የሚገኘው የመንበረ ጸባዖት ቅድስ ሥላሴ ቤ/ክ ደጃፍ ላይ የተለጠፈው ማስታወቂያ።
የዘ-ሐበሻ የስዊድን ዘጋቢ ባስተላለፈው መረጃ መሠረት ቀድሞ ገለልተኛ ሆኖ የተመሠረተው ይህ ቤተክርስቲያን በአንዳንድ መዘምራን እና የማህበረቅዱሳን አባላት አማካኝነት በተነሳ ጥያቄ የዛሬ ሁለት ዓመት የአቡነ ጳውሎስ ስም በቅዳሴ ላይ እየተጠራ ግን በገለልተኛነቱ እንዲቆይ ተወስኖ አቡነ ጳውሎስ ካረፉ በኋላም የ6ኛው ፓትሪያሪክ አቡነ ማቲያስ ስም እየተጠራ በገለልተኛነት ቆይቶ ነበር። እንደ መረጃ ምንጫችን ገለጻ ከ2 ወራት በፊት እንደገና፤ በቤተክርስቲያኑ አንዳንድ መዘምራን እና የማህበረ ቅዱሳን አባላት ባነሱት ጥያቄ ቤተክርስቲያኑን ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ስር ለማስገባት እንስቃሴ ተጀምሮ አሁን ያለው የቤተክርስቲያኑ ቦርድ በአዳዲስ ሰዎች እንዲተካ፣ የሰበካ ጉባኤውም አስተዳደር በአዲስ መልክ እንዲዋቀር፤ እንዲሁም ቤተክርስቲያኒቱ በካህናቱ እንድትመራ ጥያቄ አቅርበዋል።
በእንደዚህ ያለ ሁኔታ ውስጥ ያለው የስቶክሆልሙ መንበረ ጸባኦት ቅድስት ሥላሴ ቤ/ክ ከገለልተኛነት ወደ ኢትዮጵያው ሲኖዶስ ለማስገባት ውሳኔ እንዲሰጥ ከፍተኛ ጥረት እየተደረገ ባለበት በዚህ ወቅት ይህን ተከትሎም በቤተክርስቲያኒቱ ውስጥ ቦርዱ በመግለጫው ላይ እንዳለው ክርስቲያናዊ ያልሆኑ ሥነምግባራቶች መከሰትና ያለመግባባትም መፈጠር ጀምሯል።
የቤተክርስቲያኒቱ አስተዳደር ቦርድ እና ሰበካ ጉባኤው ይህን አለመግባባት ለማብረድ ቤተክርስቲያኑን ላልተወሰነ ጊዜ መዝጋቱን ያሳወቀ ሲሆን “ወደፊት ያለውን ሂደት ለማህበረ ምዕምናን እና ምዕመናቱ እናሳውቃለን” ብሏል።

Tuesday, December 24, 2013

Israeli Mossad agents trained Nelson Mandela in Ethiopia: Israeli archive


Israeli Mossad agents trained Nelson Mandela in Ethiopia: Israeli archive
The Indian Express:-Israeli Mossad agents operating in Ethiopia in 1962 unwittingly trained Nelson Mandela in hand-to-hand combat, weaponry and sabotage, according to a document released by Israel’s state archives.A letter from a Mossad official to the foreign ministry, dated October 11, 1962 titled “THE BLACK PIMPERNEL” and released to the public yesterday, recalls a conversation in which “we discussed a trainee in Ethiopia named David Mobasari, from Rhodesia”.”The aforementioned was trained by the Ethiopians in Judo, sabotage and weapons,” the letter read.”The Black Pimpernel” was the nickname given at the time to Mandela, the revered anti-apartheid hero and former ANC leader who died this month, while he was on the run from white South Africa during the liberation struggle.According to Haaretz newspaper, which first reported the story, the term “Ethiopians” was probably a code name for Israeli Mossad agents working in Ethiopia.”He greeted our men with (Hebrew salutation) ‘Shalom’, was familiar with the problems of (Jewish diaspora) and Israel and created the impression of an educated man,” the letter read.”The Ethiopians tried to make him a Zionist.”"It now emerges from photographs in newspapers on the arrest of the Black Pimpernel in South Africa that the trainee from Rhodesia was using a pseudonym, and the two are actually the same person,” the letter read.
According to the letter, Mandela took an interest in the methods of the Hagana and Jewish militias that existed before Israel’s creation in 1948.
The Nelson Mandela Foundation, however, said in a statement that “it has not located any evidence in Nelson Mandela’s private archive (which includes his 1962 diary and notebook) that he interacted with an Israeli operative during his tour of African countries in that year”.
Mandela “received military training from Algerian freedom fighters in Morocco and from the Ethiopian Riot Battalion at Kolfe outside Addis Ababa, before returning to South Africa in July 1962,” the foundation said.
via www.harartubes

Thousands dead in South Sudan violence, UN says

The BBC's James Copnall explains the fighting gripping the world's newest state, South Sudan - in 60 seconds
The BBC’s James Copnall explains the fighting
 gripping the world’s newest state,
South Sudan – in 60 seconds
December 24, 2013 (BBC) — Thousands of people must have been killed in the past week of violence in South Sudan, the top UN humanitarian co-ordinator there has told the BBC.
Toby Lanzer, who is in Bentiu in northern Unity state, said it had been “a devastating week for South Sudan”.
Earlier President Salva Kiir said his forces had recaptured the key town of Bor days after it was seized by rebels.
The rebels are led by Riek Machar, of the ethnic Nuer, who has been battling President Kiir, of the Dinka.
The UN earlier said that it had reports of at least three mass graves.
One was in Bentiu in the north, and two in the capital, Juba.
‘Palpable fear’
Mr Lanzer told the BBC’s Newshour programme: “I think it’s undeniable at this stage that there must have been thousands of people who have lost their lives.
“When I’ve looked at the hospitals in key towns and I’ve looked at the hospitals in the capital itself, the range of injuries, this is no longer a situation where we can merely say it’s hundreds of people who’ve lost their lives.”
The UN High Commissioner for Human Rights, Navi Pillay, said: “There is a palpable fear among civilians of both Dinka and Nuer backgrounds that they will be killed on the basis of their ethnicity.”
The UN says at least 80,000 people have been displaced by the South Sudan crisis – about half of them seeking shelter at a number of UN bases.

ሚሊየነሩ ኒቆዲሞስ ዜናዊ (ከእየሩሳሌም አርአያ)


ኒቆዲሞስ ዜናዊ የአቶ መለስ ዜናዊ ወንድም ነው። ከወ/ሮ አለማሽ ገ/ልኡልና ከአቶ ዜናዊ አስረሳኸኝ የተወለዱ ወንድማማቾች ናቸው።
ኒቆዲሞስ በደርግ ስርአት በክብሪት ፋብሪካ ተቀጥሮ በተራ ሰራተኝነት ይሰራ ነበር። የአካል ጉዳተኛ (አንድ እግሩ) የሆነው ኒቆዲሞስ ከተራ ወዝአደርነት ወጥቶ ሚሊየነር ለመሆን የበቃው ደርግ ወድቆ ሕወሐት/ኢህአዴግ ወደ ስልጣን ከመጣ በኋላ ነበር። የፋብሪካ ስራውን በግንቦት 1983ዓ.ም ማግስት የለቀቀው የአቶ መለስ ወንድም ኒቆዲሞስ ከአሜሪካ በ25ሺህ ዶላር የተገዛች አዲስ አውቶማቲክ ማርሽ አውቶሞቢል እንዲይዝ ተደረገ።

Sunday, December 22, 2013

ጉቦ በመቀበል እስረኞችን ፈተዋል የተባሉ የማረሚያ ቤት ሹሞች ታሰሩ

-እስከ 500 ሺሕ ብር ሲቀበሉ እንደነበር ተጠቁሟል
ከአዲስ አበባ ማረሚያ ቤት ከ40 ሺሕ ብር እስከ 500 ሺሕ ብር ድረስ ጉቦ በመቀበል፣ ከአምስት ዓመት በላይና በታች ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የሚገኙ ታራሚዎችን በሐሰተኛ ሰነድ ከእስር እንዲፈቱ አድርገዋል በሚል የተጠረጠሩ ሦስት የማረሚያ ቤቱ ኃላፊዎችና አምስት ግብረ አብሮቻቸው በቁጥጥር ሥር ዋሉ፡፡
የማረሚያ ቤቱ ሹሞች ኦፊሰር ገብረ መድህን አረጋ ደስታ፣ ረዳት ኦፊሰር ኢሳያስ ከበደ ገብረ ጻድቅና ዋርደር ኢብራሂም መሐመድ ሲሆኑ፣ ከውጭ ሆነው ድርጊቱን በማቀነባበር የተጠረጠሩት ደግሞ ሰለሞን ገለታ፣ ብሩክ ኃይሌ፣ ሳባ ገብረ ሚካኤል፣ ናታን ዘለዓለምና ቴዎድሮስ ግደይ የሚባሉ ናቸው፡፡ ሁሉም ተጠርጣሪዎች በፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት ሁለተኛ ወንጀል ችሎት ቀርበዋል፡፡ 
ሦስቱ የማረሚያ ቤቱ ተጠርጣሪ ሹሞች የእስረኞች አስተዳደር የሥራ ኃላፊዎችና ሠራተኞች ሲሆኑ፣ በሐሰት የተዘጋጀና ከጠቅላይ ፍርድ ቤት የተሰጠ የእስረኛ መፍቻ የሚመስል ሐሰተኛ ሰነድ በመጠቀም፣ 11 ታራሚዎችን ከ40 ሺሕ እስከ 500 ሺሕ ብር በመቀበል ከእስር እንደፈቷቸው ዓቃቤ ሕግ ለፍርድ ቤት አስረድቷል፡፡