Sunday, December 29, 2013

በሰሜን ሸዋ ዞን ሞተዋል ተብለው ፍታት ሲደረግላቸው የነበሩት አዛውንት ከሞት ነቁ

አዲስ አበባ ፣ ታህሳስ 18 ፣ 2006 (ኤፍ ቢ ሲ) በአማራ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን ሲያ ደብር ዋዩ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት የ65 አመቱ አዛውንት አቶ ሃይሉ በልሁ ከቀናት ህመም በኋላ ታህሳስ 16 ቀን 2006 ዓ.ም ህይወታቸው አልፏል ። የቅርብ ወዳጅ ዘመድ እስኪሰበሰብ ድረስም ቀብራቸው እንዲዘገይ ይደረጋል።
በአካባቢው ባህል መሰረትም ከ18 ሰዓታት ቆይታ በኋላ በባህሉ መሰረት የቤተክርስቲያን ካህናት ተገኝተው ፍታት ያደርጉላቸዋል፥ ይሁን እንጅ በዚህ ጊዜ ያልተለመደ እና እንግዳ ነገር ይከሰታል። ይኸውም ካህናቱ የሟች አስክሬን ባለበት ሳጥን ውስጥ የሰው ድምጽ እንደሰሙ በመናገር ሳጥኑ ይከፈት ዘንድ ያዛሉ።
ከሌሊቱ ስምንት ሰዓት ላይም ሞተዋል የተባሉት አዛውንት ያሉበት ሳጥን እንዲከፈት ሲደረግ፥ አቶ ሃይሉ በህይዎት ነበሩ ። ህይዎታቸው አልፏል ተብለው ለቀብር የተዘጋጁት አቶ ሃይሉ ግንዛቱን ፍቱልኝ በማለትም የሚጠጡት ውሃ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል።
ለለቅሶ የተሰበሰበው ቤተ ዘመድም በውሃ ፈንታ አጥሚት በማዘጋጀት ከሰጧቸው በኋላ አቶ ሃይሉ ደህና መሆን ችለዋል። አዛውንቱን ለመቅበር የተሰበሰበው ዘመድ አዝማድም በደስታ ተለያይቷል።
መረጃውን የሲያ ደብር ዋዩ ወረዳ መንግስት ኮሚዩኒኬሽን ጉዳዮች ፅህፈት ቤት አድርሶናል።

No comments:

Post a Comment