Monday, September 9, 2013

ሸንጎ በአዲስ አበባ የተጠራውን ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚደግፍ አስታወቀ

የሸንጎ መግለጫ፦
ሸንጎ በአዲስ አበባ የተጠራውን ሰላማዊ ሠልፍ ይደግፋል
ጳጉሜ ፪፣ ፪፼፭
September 7, 2013
ህገመንግስታዊና ተፈጥሮአዊ መብታቸውን ተጠቅመው ሰላማዊ የፖለቲካ ተሳትፎ ለማድረግ የሚጥሩ የፖለቲካ ድርጅቶችን ህወሓት/ኢህአዴግ ቀንተቀን እያጠበበው ከመጣው የፖለቲካ ምህዳር ሊያስወጣቸው የሚያደርገውን ጥረት ሸንጎ እያወገዘ፣ የተቃዋሚ ድርጅቶች የሚደርስባቸውን አስከፊ እንግልትና በደል ተቋቁመው ህዝባዊ እንቅስቃሴውን ማስቀጠላቸውን ያደንቃል።
ያለውን አምባገነን አገዛዝ ታግሎ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመፍጠር የታጋይ ድርጅቶችን አንድ ላይ መቆም ግድ የሚል በመሆኑ በነጠላ የሚደረጉ ትግሎችን በማስተባበር ትግሉን ውጤታማ ማድረግ ወደሚቻልበት ደረጃ ማድረስ አስፈላጊ ነው። አንድነት መስከረም አምስት በአዲስ አበባ የጠራውን ሰላማዊ ሠልፍ 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ ለማዘጋጀት መወሰናቸው እሰየው የሚያሰኝና ትግሉ ጥሩ አቅጣጫ ይዞ መጓዝ እንደጀመረ የሚያመላክት ነው። ይህም ትብብር ከፍወዳለ ደረጃ እንደሚደርስ ትስፋችን ነው።
የፖለቲካ ድርጅቶች እንዲህ ተባብረው በሚቆሙበት ወቅት ህዝቡም በነቂስ በመውጣት የተባበረ ጠንካራ ጉልበት እንዲፈጥር ሸንጎው ያሳስባል።
በተባበረ ትግል ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን!
Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=7163

No comments:

Post a Comment