የሸንጎ መግለጫ፦
ሸንጎ በአዲስ አበባ የተጠራውን ሰላማዊ ሠልፍ ይደግፋል
ጳጉሜ ፪፣ ፪፼፭
September 7, 2013
ጳጉሜ ፪፣ ፪፼፭
September 7, 2013

ያለውን አምባገነን አገዛዝ ታግሎ ዴሞክራሲያዊ ስርዓትን ለመፍጠር የታጋይ ድርጅቶችን አንድ ላይ መቆም ግድ የሚል በመሆኑ በነጠላ የሚደረጉ ትግሎችን በማስተባበር ትግሉን ውጤታማ ማድረግ ወደሚቻልበት ደረጃ ማድረስ አስፈላጊ ነው። አንድነት መስከረም አምስት በአዲስ አበባ የጠራውን ሰላማዊ ሠልፍ 33ቱ ፓርቲዎች በጋራ ለማዘጋጀት መወሰናቸው እሰየው የሚያሰኝና ትግሉ ጥሩ አቅጣጫ ይዞ መጓዝ እንደጀመረ የሚያመላክት ነው። ይህም ትብብር ከፍወዳለ ደረጃ እንደሚደርስ ትስፋችን ነው።
የፖለቲካ ድርጅቶች እንዲህ ተባብረው በሚቆሙበት ወቅት ህዝቡም በነቂስ በመውጣት የተባበረ ጠንካራ ጉልበት እንዲፈጥር ሸንጎው ያሳስባል።
በተባበረ ትግል ዴሞክራሲያዊት ኢትዮጵያን እንገነባለን!
Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=7163
No comments:
Post a Comment