Friday, August 30, 2013

ማኀበረ ቅዱሳን በዌብሳይቱ ላወጣው ርዕሠ አንቀጽ የተሰጠ ምላሽ


እውነት መስካሪ – ከሚኒስታ
ማቅ፡ ‘‘ ማኅበረ ቅዱሳን ከዚህ ቀደምም ከማንም በፊት በሀገራችን የአክራሪነት ዝንባሌዎች እንዳሉ በማመልከት በኩል ግንባር ቀደም ሚና ተጫውቷል፡፡ “አክራሪዎች” በተለያዩ አካባቢዎች አብያተክርስቲያናትን ሲያቃጥሉ ክርስቲያኖችን ሲያርዱ አካሔዱ መልካም አለመሆኑን በመጠቆም እርምጃ መውሰድ እንደሚገባ በማሳሰብ ሀገራዊ ሓላፊነቱን ለመወጣት ሞክሯል፡፡ የሃይማኖቶች መከባበር በመላው ሀገሪቱ እንዲሰፍን ያለውን ቁርጥ አቋምም አንጸባርቋል፡፡’’
መልስ፦ ለመሆኑ ከዚህ ቀደም በቤተክርስቲያንና በካህናት በምእመናንና በንዋይተ ቅዱሳን ላይ የደረሰውን ውድመት በርግጥ የፈጸመው ክፍል ማን እንደሆነ በምርመራ ተረጋግጦ ነው ‘አክራሪዎች’ ናቸው ብላችሁ ርምጃ እንዲወሰድ የተናገራችሁት? ድርጊቱ የኢትዮጵያን ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንን ለማጥፋት ካልቻለም ለማደከም የተነሳውን በቤተመንግስት ያለው ጸረ-ኢትዮጵያና ጸረ-ኦርቶዶክስ ኃይል እንዳላደረገው ምን ማረጋገጫ አላችሁ? አንዱን ብሔረሰብ ከሌላው ለማጋጨት ከላይ እታች ሲል የኖረና ያልተሳካለት አጥፊ ቡድን ዛሬ ደግሞ አንዱን ኃይማኖት ከሌላው ጋር ለማጋጨት የሚያደርገውን ታላቅ ሴራ እንዲሳካለት የሚያግዝ የእንካ በእንካ የቤት ስራችሁ እንዳልሆነ በምን ማረጋገጥ ይቻላል?
Short URL: http://www.zehabesha.com/amharic/?p=6911

No comments:

Post a Comment