Monday, August 12, 2013

ኦህዴድ ኢሳትን ለማስቆም እንደሚሰራ አስታወቀ

ነሃሴ ፮(ስድስት)ቀን ፳፻፭ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-ሰሞኑን የድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች በነቀምት ባደረጉት ስብሰባ ህዝቡ ኢሳትን እንዳይመለከት ካድሬዎች ከፍተኛ ስራ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

አመራሮቹ ኢሳት የአሸባሪ ድርጅቶች ንብረት በመሆኑ፣ ህብረተሰቡ ኢሳትን መመልከቱን እንዲያቆም ባለስልጣኖቹ ወትውተዋል።በስብሰባው ወቅት ለካድሬዎች ከተነገራቸው ነገር መካከል አንዱ ኢሳትን በሚመለከት ህግ ሊወጣ ነው መባሉ ነው። ምን አይነት ህግ እንደሚወጣ ግን ባለስልጣኖቹ ከማብራራት ተቆጥበዋል።ኢሳት በናይልሳት የሚያሰራጨው ስርጭቱ በአፈና እንዲቋረጥ ከተደረገ በሁዋላ ላለፉት 7ወራት  በኤስ ኢ ኤስ 5 እና በአሞስ ላይ የቴሌቪዥን ስርጭቱን እንዲሁም በተለያዩ የሬዲዮ ሞገዶች የኢትዮጰን ህዝብ እያገለገለ ይገኛል።

No comments:

Post a Comment