Saturday, January 25, 2014

ወታደራዊ መንግስቱ ታቃዋሚዋች ላይ በወሰደው የሀይል እርምጃ 50 ግብፃዊያን ተገደሉ

ለፈው ሀሙስ ባስነበብኩዋቹህ የግብፅ ዜና ዛሬ 3 አመቱን የሚያስቆጥረው ሙባረክን ከስልጣን ያባረረው የግብፃች አብዩት የተቀሰቀሰበትን 3ኛ አመት ምክንያት በማረግ መሐመድ ሙርሲን በሀይል በማንሳት ስልጣን በተቆጣጠረው ወታደራዊው የመፈንቅ ለመንግስቱ ላይ አዲስ አብዩት ለማንሳት በአኽዋን ሙስሊም ፓርቲን ጨምሮ የተለያዩ የወጣት ድርጅቶች ለዛሬ ቀጠሮ መያዛቸውን ማስነበቤ ይታወሳል ዛሬ በግብፅ የደረሰውን በጥቂቱ አስነብባቹሀለው

ዛሬ በግብፅ ህዝቦች ቀጠሮ ተይዞለት የነበረው ህዝባዊ አመፅ የመነሻ ሰአቱ ከዙህር ሰላት (6:30) በኃላ እንዲሆን በተያዘው እቅድ ሰልፍ ልክ በዛው ሰአት በመላው ግብፅ የተቀጠጠለ ሲሆን በተለይ በካይሮ ሁሉም አካባቢዋች በነገራችን ላይ ኮይሮ ወደ ጎንዋ ጠበብ ብላ በቁመት ዘለግ ያለች (ወደ 148 ኪሎ ሜትር ) የምትረዝም ከተማ ነች ከአዲስ አበባ መተሀራ ድረስ ይሆናል
ይህ ህዝባዊ እንቅስቃሴ ተደርጎል በካይሮ በተያዘው እቅድም ከካይሮ አራቱም አቅጣጫ የሚያወጣው ሰልፈኛ በሚይዳን ታህሪር እንዲገናኘ ታቅዶ የነበረ ቢሆንም ይህን እቅድ ቦታውን በ200 ታንኮች በማጠር በወታደራዊ መንግስቱ ደጋፌዋች እንዲያዝ በማረግ ላይ ሲጨፈርበት እና ለመጪው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ የመፈንቅለ መንግስቱ መሪ ሲሲ ለፕሬዝደንትነት እንዲወዳደር የመቀስቀሻ መድረክ ሆኖ አምሽቶል በሜዳነል ተህሪር ለተገኙት የ ሲሲ ደጋፌዋች በሂሊኮፕተር አበባ ሲበተን የዋለ ሲሆን በተቃራኒው ሂሊኮፕተርን ጨምሮ በታንክና ጥይት በመጠቀም በወታደራዊ መንግስቱ ታቃዋሚዋች ላይ በወሰደው የሀይል እርምጃ እስከ አሁን ባለው መረጃ 50 ግብፃዊያን የተገደሉ መሆኑ የታወቀ ሲሆን ሂልዋን በተባለችው ከተማ ብቻ 22 ሠዋች ተገድለዋል
Baba Ayedu

No comments:

Post a Comment