Tuesday, February 18, 2014

Oromia Region’s President Alemayehu Atomsa resigns/አለማየሁ አቶምሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኦሕዴድ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ፡፡

Alemayehu-Atomsa2The President of the Oromia Regional State, Alemayehu Atomsa, has resigned. His resignation has been accepted by the Executive Committee of his party, Oromo Peoples’ Democratic Organization (OPDO).
Alemayhu has been battling with severe diseases for the past few years. ESAT Television had reported that close to two million birr has been spent in his treatment from the coffers of the Ethiopian government.
የኦሮሚያ ክልል ፕሬዝዳንት አቶ አለማየሁ አቶምሳ በገዛ ፈቃዳቸው ከኦሕዴድ ሊቀመንበርነታቸው ለቀቁ፡፡በዛሬው ዕለት በተካሄደው የኦሮሞ ሕዝቦች ዲሞክራሲያዊ ድርጅት (ኦሕዴድ) ሥራ አስፈጻሚ ኮሚቴ ስብሰባ መልቀቂያቸውን ያስገቡት አቶ አለማየሁ አቶምሳ ጥያቄያቸው ተቀባይነት አግኝቶ ከሥልጣን መነሳታቸው ታውቋል፡፡አቶ አለማየሁ ቀድሞውንም ሥልጣን ሲይዙ በከባድ ሕመም የሚሰቃዩ መኾናቸው እየታወቀ ሲኾን ምንጮች እንዳረጋገጡት አቶ አለማየሁ ወደ መንፈቅ ለሚጠጋ ጊዜ በውጭ አገር በሕክምና ላይ ነበሩ፡፡ በተደጋጋሚ ኮማ ውስጥ ይገቡም ነበር ተብሏል፡፡ በዚህ ጊዜ የፕሬዝዳንትነቱን ቦታ ተክተው ይሠሩ የነበሩት አቶ አብዱላዚዝ አህመድ ሲኾኑ የኦሕዴድ ሊቀመንበርነታቸውን ሥልጣን ደግሞ የሲቪል ሰርቪስ ሚኒስትሩና የፓርቲው ምክትል ሊቀመንበር አቶ ሙክታር ከድር እንደነበሩ ምንጮች ጨምረው አረጋግጠዋል፡፡
Executive Committee of OPDO
1. Alemayehu Atomsa
2. Muktar Kedir
3. Zelalem Jemaneh
4. Girma Biru
5. Abadula Gemeda
6. Kuma Demekisa
7. Sofiyan Ahimed
8. Diriba Kuma
9. Abdulaziz Mehamed
source:http://ayyaantuu.com/

No comments:

Post a Comment