Monday, February 24, 2014

ስለ ማዕከላዊ እስር ቤት ይህንን ያውቁ ነበር?

በማዕከላዊ በሚገኙት አራቱ ዋና የማሰሪያ ብሎኮች አሉ። ሆኖም በየብሎኩ ያለው ሁኔታ በከፍተኛደረጃ ይለያያል፡፡ “ጨለማ ቤት” በመባል በሚታወቀው በጣም የከፋ ብሎክ የቀን ብርሃን እናየመፀዳጃ አገልግሎት ማግኘት በእጅጉ የተገደበ ነው። “ጣውላ ቤት” በሚባለው ብሎክ በተባይየተወረረ ነው። እስረኞቹ ለመርማሪዎቹ ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት በሚያደርጉት ትብብር መሰረትበቅጣት ወይም በማበረታቻ መልኩ መሰረታዊ ፍላጎቶቻቸውንና ሌሎች የሚያስፈልጓቸውን ነገሮችሊከለከሉ ወይም ሊፈቀዱላቸው ይችላል፡፡ ይህም ታሳሪዎቹን ከአንዱ ብሎክ ወደ ሌላ ማዘዋወርንይጨምራል፡፡ “ሸራተን” በመባል ወደሚታወቀው ብሎክ ሌላው ቀለል ያለ ድብደባ እና አካላቸውበደም ተጨማልቆ በጣም ለደከሙ ማረፊያ ቦታና ለመዛወር የተሻለ የመንቀሳቀስ እድልስለሚያስገኝ ከመፈታት ቀጥሎ እስረኞች እጅግ የሚናፍቁት ነገር ነው።

እስረኞ እርቃናቸው ሆነው እጆቻቸው ከግድግዳ ጋር ታስረው እንዲንጠለጠሉ ተደርጎ ለሶስትሰዓታት ያለማቋረጥ ይደበደባሉ።
በጨለማ ቤት እና በጣውላ ቤት የሚታሰሩ እስረኞች በተለይ በመጀመሪያዎቹ የእስር ወቅቶች የህግጠበቃ እና ዘመዶቻቸውን እንዲያገኙ አይፈቀድላቸውም፡፡ የታሰሩ ዘመዶቻቸውን ለመጠየቅበየቀኑ ወደ ማዕከላዊ ቢሄዱም ምርመራው እስኪያልቅ በሚል ለተራዘመ ጊዜ ከእስረኞቹ ጋርለመገናኘት ሃላፊዎቹ እንደማይቅዱላቸው የማይፈቀደው እስረኞቹ በስቅይ ብዛት ሰውነታቸውስለተበላሽ ነው። በምርመራ ወቅት የህግ ጠበቃ አለመኖሩ ታሳሪዎቹ ላይ የሚፈፀመውን በደልእንዲጨምር ያደርጋል፣ በመርማሪዎቹ የሚፈጸሙ ጎጂ አያያዞችና ማሰቃየትን የሚመለከቱመረጃዎች እንዳይመዘገቡ ያደርጋል።
source:Girum Zeleke

No comments:

Post a Comment