Thursday, February 20, 2014

ከድልድይ ላይ ራሷን በመወርወር ለመግደል ስትሞክር የነበረችው ወጣት ማን ትሆን? ቪዲዮዉን ይዘናል


ከዳዊት ሰለሞን
በርብርብ የተረፈችው ወጣት
ከድልድይ ላይ ራሷን በመወርወር ለመግደል ስትሞክር የነበረችው ወጣት ማን ትሆን?
ትናንት ከሰዓት አካባቢ አራት ኪሎ ለመንገደኞች መሸጋገሪያ ተብሎ በተሰራ ድልድይ ላይ የወጣች በሃያዎቹ መጨረሻ አካባቢ የምትገመት ሴት ራሷን ወደ መኪና መንገዱ ለመወርወር በምትዘጋጅበት ወቅት በአካባቢው የተገኙ ሰዎች ባደረጉት ርብርብ አደጋ ሳይደርስባት ለመትረፍ በቅታለች፡፡
ወጣቷን ለማትረፍ ሁለት የእሳት አደጋ መኪኖች ብዛት ያላቸው ፖሊሶች በስፍራው ተገኝተው የነበሩ ቢሆንም ወጣቷ ‹‹ሙስሊሞችን እወዳለሁ እነርሱን ጥሩልኝ››በማለቷ ሁለት ሙስሊም የሆኑ ሴቶች ቀርበው አነጋግረዋታል፡፡ በዚህ ቅጽበትም ሰዎች ቀርበዋት ይዘዋታል፡፡ ወጣቷን ለዚህ ውሳኔ ያበቃት ምን ይሆን?በቅርቡ ከሳኡዲ የተመለሰች ስደተኛ ትሆን? በስፍራው የነበሩ ሰዎች ይህን መሰል ጥያቄዎች እንድትመልስላቸው ይፈልጉ የነበረ ቢሆንም ፖሊሶች አጣድፈው ወስደዋታል፡፡የት አድርሰዋት ይሆን?
Ze-Habesha Website

2 comments: