Thursday, February 20, 2014

ከአውሮፕላኑ ጠለፋ በኋላ የተከናወኑ ዋና ዋና ጉዳዮች – (ዜና ትንታኔ)

ምኒልክ ሳልሳዊ እንዳጠናቀረው
የኢትዮጵያ አየር መንገድን አስተድደራዊ ብልሹነት እና የዘረኝነት አድልዎን ያማከለ የኢትዮጵያን እና የአማራን ጉዳይ ያካተተ አንገብጋቢ አጀንዳዎች ይዞ እንዲሁም በግሉ ከጀርባው አልወርድ ያሉትን የወያነ ቅማሎች ደህንነቱን የሚያበረውን አውሮፕላን በመጥለፍ አሊያም በማገት በሰላም ጀነቭ ያሳረፈው ረዳት አብራሪ ሃይለመድህን የተመለከቱ ዘገባዎች መውጣታቸውን እንደቀጠሉ ነው።
በአብዛኛው ኢትዮጵያውያን ዘንድ ድጋፍ የተቸውረው ይህንን የጠለፋ /እገታ ጉዳይ በተመለከተ የወያነው መንግስት ለውጥ የሚያደርግበት እና ለፖሊሲዎቹ አፋጣኝ አትኩሮት ሊሰጥ ይገባዋል ከሚሉ የስር አቱ ደጋፊዎች ጀምሮ እስከ የሃገሪቷን የሰብ ኣዊ መብት ጥሰቶች እያነሱ የፖለቲካው ምህዳር ጥበቱን በዘረኝነት ልይ የተመረኮዘን የኢኮኖሚ ብዝበዛውን እና የኢትዮጵያን ህዝብ ወደ ጎን ያገለለውን ስር ኣት ማስረጃ እያጣቀሱ በመተቸት ጠላፊውን የደገፉ እንዲሁም በተሰቡን ጨምሮ ጀግና እስከማለት የደረሱበት ሁነታ ተከስቷል።
እስካሁን ድረስ ጠላፊውን በተመለከተ ምንም አይነት ዝርዝር ጉዳዮችን ያልተናገረው የስዊዘርላንድ ፖሊስ አይሮፕላኑ በተጠለፈበት ሰኞ የወጡ ዘገባዎች እንደሚይመለክቱት ረዳት አብራሪው የደህንነት ስጋቶች እንዳሉበት እና በሃገሪቱን ያለው ስር ኣት የሚከተላቸው የዘረኝነት አስተዳደር እና የሃይማኖት ጣልቃ ገብነት እንዲሁም የአየር መንገዱ የአስተዳደር ብልሹነት የፈጠሩት እንደሆነ ሳይታለም የተፈታ ጉዳይ ነው።
የወያነ ስር ኣት የቅርብ ሰዎች የረዳት አብራሪውን ስም እና የበተሰቡን ስም ጥላሸት ከመቀባት ጀምሮ ጉድዩን ወደ ዘረኝነት የወሰዱትም ጠባቦች ሲኖሩ ወደ ወያነ ጠጋ ብለው ለመኖር የፈለጉም ሃይለመድህንን አብጠልጥለዋል ሆኖም አንዳቸውም አልተሳካላቸውም።….
ጉዳዩን በቅርብ እየተከትተለ ያለው የኢሳት ተለቭዥን በተሰቦቹን ወዳጆቹን ጓደኞቹን እና የአየር መንገድ ሰዎቹን በማነጋገር ሰፊ ጊዘውን ሰቷል። ያነጋገራቸው የበተሰቡ አባላት ሃይለመድህንን በመደገፍ የሃገር ጉዳይ የሚያንገበግበው ጀግና ሲሉት ወዳጆች እና ጓደኞቹ የሃይለመድህንን መልካምነት በይፋ መስክረዋል። እንዲሁም የአየር መንገዱ ሰራተኞች የሃይለመድህንን ታታሪነት እና ጸባየ ሸጋነት አረጋግጠዋል።
እንዲሁም ቢቢኤን ራዲኦ ኢትዮጵያውያን በአውሮፓ ጠበቃ እንዳቆሙረት በፕሮግራሙ ላይ ዘግቧል። የጠለፋውን ሁነታ ተከትሎ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በበረራ ደህንነት ስራ ውስጥ ለረጅም ጊዜ ያገለገለውና በክትትልና ደህንነት ስጋት ከአመት በፊት ድርጅቱን ለቆ በስዊዘርላንድ ጥገኝነት የጠየቀው ሚካኤል መላኩ ከኢሳት ጋር ባደረገው ሰፊ ቃለምልልስ፣ በድርጅቱ ውስጥ ያለውን ዘረኝነትና የአስተዳደር መበላሸት አጋልጧል።
ወጣቱ ፓይለት የተለያዩ አውሮፕላኖችን አብርሮ ልምድ ካካበተ በሁዋላ 767 የተባለውን አውሮፕላን በረዳት ፓይለትነት ለማብረር መቻሉን የገለጸው ሚካኤል፣ በዚህ ደረጃውም ከፍተኛ የሆነ ክፍያ የሚከፈለው በመሆኑ የገንዘብና የምቾት ችግር እንደማያጋጥመው ገልጿል። አብራሪው የ3 ሺ ሰራተኞችን ዋይታ ይዞ መምጣቱን የሚናገረው ሚካኤል፣ የኢትዮጵያ ህዝብ ከጎኑ ሊቆምለት ይገባል ብሎአል
የካፒቴን ሃይለመድህን የጠላፋ ምክንያት አወዛጋቢ ሆኖ በቀጠለበት ሁኔታ ፣ ካፒቴኑ ከአጎቱ ከዶ/ር እምሩ ስዩም ሞት ጋር በተያያዘ እየተረበሸ መምጣቱን አቶ አሳምነው መላኩ የተባሉ የካፒቴን ሃይለመድህንን አጎት በመጥቀስ በአሶሺየትድ ፕሬስና በክርስቲያን ሞኒተሪንግ ተዘግቧል። አዲስ አበባ የኑቨርስቲ በድረገጹ ባሰፈረው መረጃም የዶ/ር እምሩ አሟሟት መንስኤ እንግዳ እንደሆነ ጠቅሷል። ኢሳት በበኩሉ ከዘመዶቹ ባገኘው መረጃ መሰረት ዶ/ር እምሩ በሰዎች መገደላቸውን አንዳንድ የቤተሰብ አባሎች እንደሚያምኑና አጎቱን ማን ገደላቸው የሚለው ጥያቄ አለመመለሱን ዘግቧል።
ይሁን እንጅ የዶ/ር ስዩም ባለቤት ነኝ ያሉ ወ/ሮ አንጓች ቢተው ባለቤታቸው የሞቱት ታህሳስ ወር ላይ ጧት ፍላሚንጎ አካባቢ ተሳፍረው ቤተመንግስት አካባቢ ሲደርሱ ከጠዋቱ 2፡30 ላይ መሞታቸውን፣ የሞታቸውም ምክንያት በልብ ህመም ምክንያት መሆኑን በመግለጽ ሰው ገደለው ተብሎ የቀረበው ዘገባ ስህተት መሆኑን አስረግጠው ተናግረዋል። ወ/ሮ አንጓች ካፒቴን ሃይለመድህን በአጎቱ ምክንያት እንደተረበሸ ተደርጎ በሚሰጠውን አስተያየት ዙሪያም ምንም የሚያዉቁት ነገር እንደሌለ፣ ከካፒቴኑ ጋር በአመት በአል ወቅት ካልሆነ ብዙም እንደማይገናኙ ተናግረዋል።
ካፒቴን ሃይለመድህን ከአጎቱ ሞት ጋር በተያያዘ ይረበሽ ነበር በማለት መግለጫ የሰጡትን ሌላውን አጎት አቶ አሳምነውን ለማግኘትና ማብራሪያ ለመጠየቅ የተደረገው ሙከራ አልተሰካም። በጉዳዩ ዙሪያ አስተያየቱን የጠየቅነው ዘጋቢያችን፣ ዶ/ር ስዩም በልብ ህመም መሞታቸውን ካፒቴን ሃይለመድህን የሚያውቅ ከሆነ፣ የሚጨነቅበት ምክንያት አይኖርም፣ ከአጎቱ ሞት ጋር በተያያዘ የሚሰጠው አስተያየትም ትክክል ላይሆን ይችላል ብሎአል።
ጠላፊው አውሮፕላኑን ወደ ጄኔቭ ከመውሰዱ በፊት ሮም ላይ ማረፉን የገለጸቸውን ዜና በተመለከተ አንዳንድ አስተያየት ሰጪዎች አውሮፕላኑ ሮም ላይ እንዳላረፈ በመግለጽ አስተያየታቸውን የገለጹ ሲሆን፣ ኢሳት በድጋሜ ተሳፋሪዋን ባነጋገረበት ወቅት፣ በአቋሟ በመጽናት አውሮፕላኑ ሮም ላይ አርፎ ወደ ሚላን ሲያቀና መጠለፉን፣ የበረራ ትኬቱዋን ለኢሳት በመላክ ትክክለኛ መረጃ መስጠቱዋን በድጋሜ ተናግራለች።
ጉዳዩ እንዴት ሊሆን ይችላል ስንል ጥያቄ ያቀረብንለት ሚካኤል መላኩ አውሮፕላኑ ሮም ላይ አርፎአል በሚል የተላለፈው ዘገባ ትክክለኛ ነው ብሎ እንደሚያምን የአየር መንገዱን አሰራር በመግለጽ አስረድቷል
የመንግስት የኮሚኒኬሽን ጽ/ቤት ሃላፊ የሆኑት አቶ ሬድዋን ሁሴን አውሮፕላኑ ካርቱም ላይ ማረፉን ፣ ቀጥሎ ደግሞ ካርቱም ላይ ማረፍ የነበረበት ቢሆንም ተጠልፎ ማረፍ ሳይችል ቀረ ብለው የገለጹት የአየር መንገዱን አሰራር ሳይዉቁ የተናገሩት አሳፋሪ ንግግር ነው ብለዋል። በአየር መንገድ የበረራ ታሪክ አውሮፕላኑ በቀጥታ ከአዲስ አበባ ወደ ሮም እንደሚያርፍ በመግለጽ ካርቱም ላይ ማረፍ ነበረበት የሚለውም ትክክል አይደለም ብሎአል።
አለማቀፍ የመገናኛ ብዙሃን ፓይለቱ አውሮፕላኑን ይዞ ጄኔቫ ላይ በመሽከርከር ለማስፈራራት ሙከራ አድርጎ ነበር በማለት ዘገባዎችን አቅርበዋል። ይሁን እንጅ እንደ ሚካኤል ገለጻ ማንኛውም አውሮፕላን ከማረፉ በፊት ነዳጅ ማቃጠል ስለነበረበት ፓይለቱ ይህን ማድረጉን እንዲሁም ለ10 ደቂቃ ጉዞ ብቻ የሚበቃ ነዳጅ ነበረው ተብሎ በመገናኛ ብዙሃን የቀረበውም ትክክል ያልሆነና በአየር መንገዱ ህግ መሰረት ለ2 ሰአት በረራ የሚያበቃ መጠባበቂያ ነዳጅ እንደሚይዝ ገልጿል።
Ze-Habesha Website

No comments:

Post a Comment