Wednesday, February 26, 2014

የአዲስአበባ የ24 ሰዓታት የቴሌቭዥን ስርጭት እቅድ ተግባራዊ መሆን አልቻለም

የአዲስአበባ ከተማ አስተዳደር የመገናና ብዙሃን ኤጀንሲ የመረጃ ውጤቶችን ለሕዝብ ተደራሽ ያደርግልኛል በሚል ከፍተኛ በጀት በመመደብ ባለፉት ዓመታት በአዲስአበባ ማዘጋጃ ቤት ሕንጻ ውስጥ ዘመናዊ ስቱዲዮና መሳሪዎች ግንባታና ግዥ ቢያከናውንም የ24 ሰዓታት ቴሌቪዥን አገልግሎት ዕቅዱን በአቅም ማነስ ምክንያት ማሳካት ሳይችል ቀርቷል፡፡

የኦሮሚያ፣ የአማራ እንዲሁም የሶማሌ ክልሎች በዓረብ ሳተላይት ላይ ጭምር የክልሎቻቸውን ዜናዎችና መረጃዎች በቴሌቪዥን እያሰራጩ ሲሆን የአዲስአበባ አስተዳደርም በተመሳሳይ መንገድ የቴሌቪዥን ፕሮግራም ስርጭቱን ከ6፡30 ሰዓት ወደ 24 ሰዓታት ፣ራዲዮ ፕሮግራሙን ስርጭት ከ18 ሰኣታት ወደ 24 ሰዓታት ለማሳደግ ባለፉት ሁለት ዓመታት ጥረት ሲያደረግ መቆየቱን የአስተዳደሩ ምንጮች አስታውሰዋል፡፡


የመሳሪያዎች ግዥና ተከላ፣ የቢሮ ዝግጅት፣ የሰው ሃይል ቅጥር ቢጠናቀቅም በታህሳስ ወር በ2006 ይጀመራል ቢባልም በይፋ ባልተገለጸ ምክንያት ስራው ሳይጀመር ቀርቷል፡፡
የአስተዳደሩ ምንጮች እንደሚናገሩት የቴሌቪዥንና የራዲዮ ስርጭቱን ማሳደግ ያልቻለው ኤጀንሲውን የሚመሩ ሙያው የሌላቸው ካድሬዎች አቅም ማነስ ጋር የተያያዘ ነው፡፡
ኤጀንሲው በያዝነው ኣመት ዕቅዱ የ2007 ዓ.ም ሃገር አቀፍ ምርጫን ዴሞክራሲዊ እና የህዝብ ተሳትፎን ለማረጋገት የሚያስችሉ የኮምኒኬሽን ስራዎች በብቃት እንዲተገበሩ ማድረግ፣ በዋና ዋና ወቅታዊ ጉዳዮች ላይ በህዝቡና በከተማ አስተዳደሩ መካከል መግባባትና መተማመን የሚፈጥሩ የኮምኒኬሽን ስራዎችን ማከናወን ከያዛቸው ዕቅዶች ግንባር ቀደሞቹ ነበሩ፡፡
በአሁኑ ወቅት በ1991 ኣ.ም የወጣው የብሮድካስት አዋጁ የራዲዮና ቴሌቭዥን ጣቢያ በግል ማቋቋምን የፈቀደ ቢሆንም ኢህአዴግ መራሹ መንግስት “የሕዝቡ ንቃተ ሕሊናው አላደገም” በሚል አዋጁን ካለመተግበሩም በላይ ኢቲቪን የተለያዩ ፕሮግራም አልባ ቻናሎች እንዲከፍት በማድረግ እንዲሁም ክልሎች በዓመት ከሚመደብላቸው አነስተኛ በጀት ቀንሰው ለቴሌቪዥን የሳተላይት ስርጭት የኪራይ ክፍያና የማሰራጫ መሳሪያዎች ግዥና ተከላ ከፍተኛ ወጪ እንዲያወጡ እያበረታታቸው መሆኑና ክልሎችም በፉክክር ውስጥ መግባታቸው ታውቋል።
በሌላ ዜና ደግሞ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የከንቲባ ጽ/ቤት ቅጥር ግቢ የሚሰሩ የከተማ አስተዳደሩ ሰራተኞች በግቢው የጸጥታ ዴስክ በኩል ከፍተኛ ፍተሻ እየተደረገባቸው ነው፡፡
በከተማ አስተዳደሩ የሚሰሩ የተለያዩ የዕለት ከዕለት ፖለቲካዊ ተግባራት በመኖራቸውና ከህዝቡ ልማታዊ እንቅስቃሴ ጋር የሚተሳሰሩ ቀጥተኛ መረጃዎች ሲያጋጥሙ በተደጋጋሚ ለኢሳት መረጃ በመድረሱና ህዝቡ እንዲያውቀው መደረጉን ተከትሎ ከተማ አስተዳደሩ ያልወደደው በመሆኑ የመረጃ ልልውጡን ለማስቀረት በሚያመች መልኩ በሚመስል ሁኔታ ከቁልፍ ባለስልጣናት በስተቀር፣ ወደ ግቢ የሚገቡ ሰዎች፣ የውስጥ ሰራተኛችን፣የውጭ የከተማ አስተዳድሩ ሰራተኞችን፣ ለተለያየ ጉዳይ የሚመጡ ባለጉዳዮችና ሌሎችም ሰዎች ጭምር ወደ ግቢው ሲመጡ ከወትሮው በተለየ ሁኔታ መታወቂያቸው በጥንቃቄ ታይቶ መኪኖቻቸው ጭምር በሚገባ ተፈትሾ እንዲገቡ እየተደረገ ነው፡፡
የተለያዩ መረጃዎች እየወጡብን ነው የሚለውን ስጋት ለማስቀረት ተብሎ በር ላይ በፈረቃ በሚቆሙ የጥበቃ ፖሊሶች የሚሰሩ ሲሆን የፍተሻውን ምክንያት ተከትሎ በተለይ የውስጥ ሰራተኞቻቸው ጧት ለስራ ሲገቡ ብዙ ሰዓት ስለሚቆሙ በከፍተኛ ምሬት ውስጥ ናቸው፡፡
ከዚህ በፊት በግቢው ውስጥ ከሚገኘው የሰራተኞች መመግቢያ አዳራሽ ብዙ ሰራተኛች ወደ ግቢው መጥተው ምሳ ላይ ለመጠቀም ይፈቅድላቸው የነበሩት የከተማ አስተዳድሩ የውጭ ሰራተኞች የፍተሻውን ስራ ጫና ለመቀነስ ሲባል እንዳይገቡ ተደርጓል፡፡
የጥበቃ ፖሊሶች የውስጥና የውጭ ሰራተኞችን መለየት ባለመቻላቸው ና ማንም ሳይፈተሽ መግባት እንደማይችል ስለተነገራቸው የመስተዳድሩ ሰራተኞች ጧት ከቤታቸው ሲወጡ መርሳት ከሌለባቸው ዋነኛ ነገር መታወቂያ ሆኗል፡፡
Source: Ethsat

No comments:

Post a Comment