Tuesday, February 25, 2014

ኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ በአባይ ግድብ ግንባታ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለው ሪፖርተር ዘገበ

ጋዜጣው በእሁድ እትሙ እንደገለጸው ኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ ” በህዳሴው ግድብ ላይ 60 ከመቶውን የትራንስፖርት፣ ሎጂስቲክና አፈር የማንሳት ሥራዎችን ከሳሊኒ በተቋራጭነት በመውሰድ እየሠራ እንደሚገኝም ባለፈው አመት ኩባንያው በቀድሞው ጠ/ሚንስትር መለስ ዜናዊ ባለቤት ወ/ሮ አዜብ መስፍን የእህት ልጅ በወ/ሮ አቲኮ ስዩም አምባየ መመስረቱን ፣ በግልገል ጊቤ አንድ እና ግልገል ጊቢ ሁለት የሀይድሮ ኤሌክትሪክ ፕሮጀክቶች ስሚንቶ እና የግንባታ እቃዎችን እንዲሁም ከፍተኛ ማሺነሪዎችን በማቅረብ መሳተፉን ዘግቦ ነበር። ይህ ኩባንያ በአባይ ግድብ ግንባታ ዙሪያ ከሳሊኒ በመቀጠል ከፍተኛውን ድርሻ መያዙን በወቅቱ ኢሳት ዘግቧል።

“ኦርኪድ ቢዝነስ ግሩፕ፣ በደረጃ አንድ ተቋራጭነቱ በአየር ማረፊያ፣ በመንገዶች፣ በሕንፃ ግንባታ፣ በነዳጅ ቁፋሮ ሥራዎችና በሌሎችም መስኮች መሰማራቱን የገለጸው ሪፖርተር፣ በእህት ኩባንያዎቹ በኩል በአበባ እርሻ፣ በትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መስኮች ሲሠራ የቆየ አገር በቀል ኩባንያ ነው፡፡ ” ብሎአል ሪፖርተር።
ወ/ሮ አቲኮ ኢህአዴግ አዲስ አበባን ሲቆጣጠር ከአንድ አነስተኛ የኪራይ መኪና ውጭ ይህ ነው የሚባል ሃብት አልነበራቸውም። ግለሰቡዋ በአጭር ጊዜ ውስጥ የናጠጡ ሀብታም ለመሆን የቻሉት በወ/ሮ አዜብ መስፍን ድጋፍ እንደሆነ ጉዳዩን በቅርበት የሚያውቁ ሰዎች ይናገራሉ፡
ጋዜጣው እንደዘገበው ወርኪድ ከጀርመኑ ባወር ኩባንያ ጋር በመነጋገር ከባድ ማሽነሪዎችን ወደ አገር ውስጥ በማስገባት ከአባይ ግድብ እስከ ነዳጅ ፍለጋ ስራዎች ያሉ ቁፋሮዎችን ያካሂዳል።
Source: Ethsat

No comments:

Post a Comment