Wednesday, April 10, 2013

በፍኖተሰላም ከተማ የሚገኙ ተፈናቃዮች ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ እንዲመለሱ እየተደረገ ነው


ሚያዚያ (አንድ) ቀን ፳፻፭ /
ኢሳት ዜና:- ዛሬ ሊነጋጋ ሲል 20 በላይ መኪኖች የፍኖተ-ሰላም ከተማን ማጨናነቃቸውን የተናገሩት ተፈናቃዮች፣ ከብር-ሸለቆ የመጡ የፌደራል ፖሊስ አባላት ከዞን እና ከወረዳ ፖሊስ አባላት ጋር በመተባበር፣ ተፈናቃዮቹ ወደ መኪኖቹ እንዲገቡ አዘዋል።
ጥሪው ድንገተኛ የሆነባቸው ተፈናቃዮች የሚያደርጉት ጥፍቷቸው ሲላቀሱ ወላጆቻቸውን ተከትሎም ህጻናት ሲያለቅሱ ይታዩ እንደነበር የአይን እማኞች ይናገራሉ።
አንድ ሌላ ተፈናቃይ ዛሬ ስላጋጠማቸው ነገር ሲናገሩሰው በተወለደበት አገር  ይህን አይነት በደል ይደርስበታልብየ አላስብም ነበር ብለዋል።
ወደ መጣበት ቦታ ለመመለስ በመጠባበቅ ላይ የነበረ አንድ ወጣት ቤቱ መቃጠሉን ቢገልጽም መንግስት እንዳደረገ ያድርገን በማለት  እንደሚሄድ ገልጿል።
ወደ መጣበት ቦታ ለመመለስ ፈቃደኛ ያልሆነ አንድ ተፈናቃይ፣ ለምን እንደማይመለስ ሲጠየቅበእርሱና በልጆቹ ላይ ለሚደርስበት ጉዳት ዋስትና ስላልተሰጠውመሆኑን ገልጿል። 2 ልጆች አባት መሆኑን የገለጸው አርሶአደሩ የልጆቹ እናት በህመም ምክንያት ራቅ ወዳለ ቦታ በመሄዷ፣ ልጆቹን ይዞ ለመመለስ አለመድፈሩን ተናግሯል።
በዛሬው እለት 16 መኪኖች ወደ ቤንሻንጉል ጉሙዝ ያቀኑ ሲሆን፣ በነገው እለትም ተጨማሪ ሰዎች ይሄዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።
ተፈናቃዮች ስለሚያቀርቡት አቤቱታ የዞኑን የጸጥታ ሀላፊ ለማነጋገር በተደጋጋሚ ስልክ ብንደውልም ስብሰባ ላይ ናቸው በሚል ምክንያት ለማነጋገር ሳይቻል ቀርቷል።
ይህ በእንዲህ እንዳለ በኖርዌይ የሚገኙ ኢትዮጵያውያን በአማራ ተወላጆች ላይ የተወሰደውን እርምጃ በማውገዝ  ሰላማዊ ሰልፎችናንና  የተለያዩ ዝግጅቶችን እንደሚያደርጉ ታውቋል።
ስርክአዲስ ታየ ተጨማሪ ዘገባ ልካለች።

No comments:

Post a Comment