Wednesday, October 1, 2014

ዲቪ 2016 ከመስከረም 21 (ኦክቶበር 1) ቀን ጀምሮ መሞላት ይጀምራል

(ዘ-ሐበሻ) የአሜሪካ መንግስት የተለያዩ ሃገራት ዜጎች ወደ ሃገሩ ገብተው እንዲኖሩና እንዲሰሩ የሚፈቅድበት የዲቪ ሎተሪ ከመስከረም 21 ቀን ጀምሮ እስከ ጥቅምት 20 ቀን 2007 ዓ፣ም መሞላት እንደሚጀምር ዘ-ሐበሻ ከስቴት ዲፓርትመንት ያገኘችው መረጃ አመለከተ።
dv-lottery
ምናልባት የኢንተርኔት መስመር መጨናነቅ ስለሚኖር አመልካቾች እስከመጨረሻው ሰዓት ድረስ መጠበቅ የለባቸውም ያለው የስቴት ዲፓርትመንቱ ማሳሰቢያ በእድሉ መጠቀም የሚፈልግ ካለ በጊዜ ማመልከቻውን መሙላት አለበት ብሏል።
ባንግላዲሽ፣ ብራዚል፣ ካናዳ፣ ቻይና፣ ኮሎምቢያ፣ ዶሚኒካን ሪፐብሊክ፣ ኢኳዶር፣ ኤልሳልቫዶር፣ ሃይቲ፣ ሕንድ፣ ጃማይካ፣ ሜክሲኮ፣ ናይጄሪያ፣ ፓኪስታን፣ ፔሩ፣ ፊሊፒንስ፣ ደቡብ ኮሪያ፣ ኢንግላንድ (ከሰሜን አየርላድ ውጭ)ና ቬትናም ባለፉት 5 ዓመታት ከ50 ሺህ ላይ ስደተኞች ወደ አሜሪካ ስለገቡ የዲቪ 2016 ባለ ዕድል ተጠቃሚ እንደማይሆኑ ስቴት ዲፓርትመት አስታውቋል። ይህም ማለት ኢትዮጵያውያን ይህን ሎተሪ መሙላት ይችላሉ።
የኢትዮጵያ መንግስት የሚያስተዳድረው የኢትዮጵያ ፖስታ አገልግሎት ድርጅት የዲቪ ፎርም እንደሚሞላ በየከተማው በተለጠፉ ማስታወቂያዎችና በሚዲያ ላይ እያስተዋወቀ ይገኛል።

የዲቪ ሎተሪ 2016ን ለመሙላት አድራሻው የሚከተለው ነው።
http://www.dvlottery.state.gov/
Entries for the DV-2016 DV program must be submitted electronically at www.dvlottery.state.gov
between noon, Eastern Daylight Time (EDT) (GMT-4), Wednesday, October 1, 2014, and noon, Eastern
Standard Time (EST) (GMT-5), Monday, November 3, 2014. Do not wait until the last week of the
registration period to enter, as heavy demand may result in website delays. No late entries or paper
entries will be accepted. The law allows only one entry by or for each person during each registration
period. The Department of State uses sophisticated technology to detect multiple entries. Individuals
with more than one entry will be disqualified.

No comments:

Post a Comment