Monday, August 25, 2014

የኢሳት ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና እህት የግፍ ሰለባዋ

10645174_704513272957683_171991983121885364_nዛ አስቂኝና ጥርስ የማታስከድን ወጣት ናት። ከእሷ ጋር ለደቂቃ አይደለም ለሰዓታት አብረህ ብታሳልፍ አይሰለችህም፤ በሳቅ ታንከተክትሃለች። አነጋገሯ ፈጠን..ፈጠን ያለ ነው። ..የሷ ቀልዶች አይረሱኝም።..በ1998 ዓ.ም የደረሰባት ነገር እጅግ አሳዛኝ ነው። የተቃዋሚ አመራሮች፣ ጋዜጠኞች፣ የቅንጅት ደጋፊዎችና ሰላማዊ ዜጎች በጅምላ እስር ቤት ሲጋዙ አጋጣሚ ጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ለሁለት ወር ገደማ እጁን ሳይሰጥ ተሰውሮ ነበር። የገዢው ባለስልጣናት (በረከትና መለስ ናቸው) ያሰማሯቸው ደህንነቶች ሲሳይን ፍለጋ ብዙ ሲማስኑ ነበር። ያላሰሱትና ያልተከታተሉት ሰው የለም፤ በመጨረሻ ግን እህቱን አፈኑ። እየደበደቡ ወደ ወለጋ ወሰዷት። ሴት ልጅ ልትቋቋመው ከምትችለው በላይ በዱላ አሰቃይዋት። « ሲሳይ የት ነው ያለው? ተናገሪ?» ሲሉ ፍዳዋን አስቆጠሯት። ምንም እንደማትውቅ ነገረቻቸው። ምንም ሲያጡ ወለጋ ላይ ፀጉሯን ላጭተው፣ በድብደባ ጐድተውና አቁስለው፣ እጅግ አዳክመው ጫካ ውስጥ አውሬ እንዲበላት ጥለዋት ሄዱ። ራሷን የሳተችው አቦነሽ (ቴሌ) ፈጣሪ ነፍስሽ ይትረፍ ሲላት ገበሬዎች አገኟት። ተሸክመው ወሰዷት። በመኖሪያ ጐጆዋቸው እንድታገግም አደረጉ። ከዚያም ስልክ ወደ አዲስ አበባ አስደወሉላት። ጋዜጠኞች ስፍራው ድረስ ሄደው አመጧት። ..እነሆ ከ8 ዓመት በኋላ ሌላ ክስ ከሙያ ባልደረቦችዋ ጋር ተመሰረተባትና በዚህ ሰሞን አገር ጥላ ተሰደደች። ይህ ግፍ መቆሚያው የት ይሆን!?…ስለተሰደዱት ጋዜጠኞች እመለስበታለሁ።
(በፎቶው የሲሳይ አጌና እህት በመሆኗ ብቻ በ1998ዓ.ም የተፈጸመባት ግፍ ይህን ይመስላል)
Source- freedom4ethiopia.

Monday, August 18, 2014

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾችን ሊያደራጅ ነው

facebook
=================ነቢል አህመድ ዘገፈርሳ=====================
ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት እና ነጻነት ለመሸራረፍ ብሎም ለመበታተን ከሚጠቀምባቸው ዘዴዎች አንዱ በማህበራዊ ድህረገጹ ያሰማራቸውን ከተቃዋሚ ሃይላት ጋር ተመሳስለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት መስለው የተቃዋሚ ሃይሎችን ሎግ በመጠቀም እንዲሁም ለሽፋንነት በየመሃሉ የተቃዋሚ ድርጅቶችን መግለጫ እንደወሽመጥ በማስገባት በማታለል እና በማጭበርበር ላይ ተመስርተው ሲሰሩ የነበሩ ስም አጥፊ ገጾችን/ ፔጆችን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በዚህ ሳምንት እረፍት እንዲወስዱ ያደረጋቸው መሆኑ ታውቋል።
ስም በማጥፋት ለውጥ ፈላጊ ሃይሎች በተለያዩ አክቲቪስቶች ላይ መጠራጠር እንዲያሳድሩ እና ጠቃሚ የተባሉ ጦማርያንን እንዲያጡ እና ትግሉ አቅጣጫውን እንዲስት በስፋት አዲስ የአሰራር ዘይቤ ለመቀየስ የተሳዳቢዎች የተዛልፊዎች እና የስም አጥፊዎች የማህበራዊ አካውንት እና ፔጆች እረፍት ላይ መሆናቸውን እና በተጠናከረ መልኩ ወደ ስራ እንደሚመለሱ በቅርብ የሚያውቋቸው ወዳጆቻቸው ተናግረዋል።
በዚሁም መሰረት በዜጎች መካከል ከባድ ጥርጣሬን ያጭራሉ የተባሉ የፈጠራ ጽሁፎች እና የሞቱ ሰዎች ፎቶዎችን በመጠቀም የተለያዩ የፌክ ወንጀሎችን በመጻፍ እንድሁም ከብልግና እና የሰውን ክብር ከሚያዋርዱ አዳዲስ ብካይ የሃሰት መረጃዎች ጋር ወዘተ ተያይዘው ወደ ማህበራዊ ድህረገጾች እርፍታቸውን ጨርሰው እንደሚመጡ ታውቋል።
Source: Zehabesha

Sunday, August 17, 2014

መሬት ላይ ያለን እዉነት በመሸሽ ለዉጥ ማምጣት አይቻልም፡፡

በርእስ እንደተጠቀሰዉ መሬት ላይ የምናየዉ ኢትዮጵያ ዉስጥ ወያኔ ስልጣን ላይ ከመጣ ከ1983 ጀምሮ የብሄር ጥያቄ ፈንድቷል፤ ይህ የማይካድ እዉነት ነዉ፡፡ ይህንን የፈነዳ እዉነት መሸሽ ወይም ያለመስማት መፈለግ የብሄርን ጥያቄ ለሚያነሱ ቡድኖችም ሆነ የፖለቲካ ድርጅቶች የሚደርስባቸዉ ትችት እና መገለል ቀላል አይደለም፤ መተቸቱም፤ ማግለሉም ወይም ማጣጣሉ መፍትሄ አይሆንም ይልቁንም መዉጣት ወደማንችለዉ ችግር ዉስጥ ይከተናል፡፡
ኢትዮጵያ እንደ ሀገር አንድትቀጥል ወይ እንድትቆም ከተፈለገ የብሄር ጥያቄን መመለሱ የግድ ነዉ፡፡ ማድበስበሱ ማለባበሱ ከዚህ ችግር እንድንወጣ አያደርገንም፡፡ እንደዉም ይህንን ጥያቄ በመመለስ ዘለቄታ ያለዉ ሰላም አንድነት እና  ህብረትን ማጠናከር ይቻላል፡፡ ምክንያቱም ኢትዮጵያ የብዙ ብሄረሰቦች ሀገር፤ ብዙ ቋንቋ እና ባህል ያላቸዉ ህዝቦች የሚኖርባት ሀገር፤ ከልዩንት ይልቅ ብዙ የሚያስተሳስሩን የጋራ የሆኑ እሴቶች ያሉን ህዝቦች ነን፡፡ ስለዚህም ጥቂቱን ጥያቄ በመመለስ ብዙ የሆኑ የጋራ ነገሮቻችንን በማዳበር አንድ ላይ ኢትዮጵያን መገንባት እንችላለን፡፡
አሁን እንደሚታየዉ ከሆነ የጋራ የሆነ ነገራችንን ለማክበር በሚል የተናጠል የሆነዉን መብት መርገጥ ዉጤቱ አሉታዊ መሆኑ የማይቀር ነዉ፡፡ ከላይ እንደጠቀስኩት የብሄር ጥያቄ ኢትዮጵያ ዉስጥ ፈንድቷል፡፡ ይህንን የፈነዳ እሳት መልስ ማዳፈን አይቻልም፤ የሚቻለዉ እነዚህን የብሄር ወይም የማንነት ጥያቄ በመመለስ ኢትዮጵያዊነት ማፅናት ይቻላል፡፡ ካለሆነ ግን እንደ ምስራቅ አዉሮፓ እነደ ኤዢያ ሀገራት ሶቬትህብረት መፈራረስ በኋላ እንደትንንሽ መንደር መሆን ወይም አፍሪካ ስንመጣ ደግሞ እንደ ጅቡቲ፤ፑንትላንድ፤ኤርትራ አይነት ትንንሽ ሀገር እንዳንሆን ስጋቴ ነዉ፡፡ ምክንያቱም የኦጋዴን፤ የአፋር፤ የኦሮሚያ፤ የሲዳማ፤ የአደሬ፤የጋምቤላ...ወዘተ የብሄር ማንነት ጥያቄ ችግሮች አሉና ነዉ፡፡
እንደኔ ምኞት ቢሆን አይደለም ኢትዮጵያ ምስራቅ አፍሪካም አንድ ብንሆን እመርጣለሁ፡፡ እንደዉም ከዚያም አልፎ አንድ ትልቋን አፍሪካን ብንሆን እመርጣለሁ፡፡ይህ ግን በምኞት ብቻ ሳይሆን በተግባርም በሚገለጥ ማሳያም ነዉ፡፡ለምሳሌ፡- የጋራ የሆኑ ትስስሮች እንዲኖሩ በማድረግ፤ በንግድ፤ የጋራ የሆነ ገንዘብ በማተም፤ የጋራ የሆነ ህብረ-ብሄር ጦር በማደራጀት ...ወዘተ፡፡ ብቻ በዛም ሆነ በዚህ የበለጠ ልንቀራረብ፤ ልንተሳሰር ሊያደርጉን የሚችሉ ነገሮችን በመፍጠር በሰላም አብረን መኖር እንድንችል ማድረግ ዉጤቱ ያማረ ነዉ፡፡
ያለበለዚያ ግን አሁን በቅርብ እዚሁ በዲያስፖራዉ ፖለቲካ እንደሚታየዉ በፓል ቶክ ሩሞች(paltalk rooms) የመከፋፈል፤ የመጠላለፍ፤ አንዱ አንዱን ሊጥል የሚደረገዉ ሩጫ መታዘብ ይቻላል፡፡ መቼም እንደሚታወቀዉ ፓል ቶክ (paltalk) በሁሉ አለም ያሉ ወገኖችን የሚያገናኝና ስለ ሀገሩ፤ ስለወገኑ ግድ የሚለዉን ብሶት ማስተነፈሻ ብቻ ሳይሆን፤ የተለያዩ ገንቢም አፍራሽም ሀሳቦች የሚንሸራሸሩበት እደሆነ ይታወቃል፡፡ እነዚህ ሩሞች ከመለያየት ቢቻል ሊያስማሙን ከሚችለዉ የጋራ ጠላት በሆነዉ በሀገር ህልውና ላይ ችግር እየፈጠረ ያለዉን የወያኔ መራሽ ስርአት ለመገርሰስ ልዩነትን ወደጎን በመተዉ በጋራ መተባበር ነበረባቸዉ፡፡ ነገርግን እንደሚፈለገዉ ሳይሆን በተቃራኒዉ አንዱ አንዱን ለመጣል መታተር የእለት ስራቸዉ ነዉ፡፡ልዩነቶቻችን በበዙ ቁጥር ለገዢዉ መንግስት ስልጣን ላይ መቆየት፤ በህዝብ ላይ የጭቆና ቀንበሩን ለመጫን ጥሩ አጋጣሚ ነዉ፡፡አሁንም ሳይረፍድ እና የባሰ ችግር ዉስጥ ሳንገባ የጋራ ችግሮቻችንን በጋራ እንፍታ፡፡የተለያዩ የብሄር ጥያቄዎቻችን ይመለሱ፤ በጋራ በመግባባት ኢትዮጵያን መገንባት ይቻላል፡፡ በትልቁ የህዝብ ዉክልና የሌለዉን፤ በጉልበት በመሳሪያ ሀይል እያስፈራራ እና እየገደለ ያለዉን ወያኔን ከስልጣን ማዉረድ የሚቻልበትን መንገድ እናጠናክር የእለቱ መልክቴ ነዉ፡፡
መስፍን ሀብተማርያም ነኝ፡፡
አስተያየት ለመስጠት:- mesfinabt@gmail.com እገኛለሁ፡፡ 

Wednesday, August 13, 2014

Ethiopian Government to Bring Criminal Charges Against Six Weeklies

Ethiopia’s justice ministry has announced that it is bringing criminal charges ranging from “dissemination of false rumours with the intent of overthrowing the government” to “undermining public trust in the government and attempts at fostering ethnic and religious divisions” against six news weeklies.
In a communiqué released on 5 August, the ministry accused the six weeklies – Lomi, Enqu, Fact, Jano, Addis Guday and Afro-Times – of “encouraging terrorism, endangering national security, repeated incitement of ethnic and religious hate, and smears against officials and public institutions.”
Two of the weeklies, Addis Guday and Fact, are among Ethiopia’s leading privately-owned newspapers and have often covered events or published stories that have generated political controversy. One of Addis Guday’s journalists, Asmamaw Hailegiorgis, has been held on a terrorism charge since 25 April.
The ministry said it had been “patient” with the six weeklies but had finally decided to bring charges in response to public pressure for corrective action. It also warned that it was ready to bring charges against other publications engaging in similar “subversive” activity.
Prime Minister Hailemariam Desalegn’s government must end the harassment of independent media that it has been orchestrating for the past few months,” said Reporters Without Borders secretary-general Christophe Deloire.
With the 10 journalists and bloggers already accused of terrorism and now this prosecution threat, the government is sending a much tougher message to news providers. Prosecuting journalists for ‘undermining public trust in the government’ is totally illegitimate.
Ethiopia is ranked 143rd out of 180 countries in the 2014 Reporters Without Borders press freedom index.
-- -- ---

Ethiopia’s “Terrorist” Journalists and Bloggers


n-PRISON-CELL-large- A cursory glance at the headlines shows that Ethiopia has one of Africa’s fastest growing economies. But the noise generated by the hyperbolic international media is drowning out the critical voices.
Political opposition is being strangled by the authorities as activists and journalists are arrested and thrown into jail at a dizzying pace.
On April 25 of this year, the Ethiopian government made news by arresting six bloggers and three freelance journalists. Setting a dangerous precedent for other governments in the region and beyond, authorities are now targeting youth online.

Sunday, August 10, 2014

ሬድዋን ሁሴን ማናቸዉ? አሁን ላሉበት የፓለቲካ ስልጣን እንዴት በቁ?

ሙሉ ስማቸው ሬድዋን ሁሴን ይባላል፡፡ በ1987ዓ.ም ከአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ በባይሎጂ ከተመረቁ በኋላ በጂንካ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ለጥቂት ጊዜ አስተምረዋል፡፡ ከጂንካም ለቀው በአዲስ አበባ አወሊያ ትምህርት ቤት ማስተማር እንደጀመሩ የህይወት ታሪካቸው ይነግረናል፡፡ አወሊያ ት/ቤት በነበሩበት ጊዜም ነው ፖለቲካን ከታች ሀ፣ ሁ፣ ሂ… ብለው መቁጠር የጀመሩት፡፡ የሬድዋን የፖለቲካ ሀ፣ ሁ፣ ሂም የተመሰረተው በሀገራዊ ጉዳይ ላይ ሳይሆን በስልጤ ህዝብ ማንነት ላይ ነበር፡፡ እናም ስልጤ በዞን ደረጃ ባለመዋቀሩ ከአካባቢው ተወላጆች ጋር ሲገናኙ ይቆጩና ይብሰከሰኩ ጀመር፡፡ በእርግጥ ጥያቄያቸው ተገቢ ሊሆን ይችላል፡፡ ሆኖም ይህችን ካርታ ብቻ መዞ ፖለቲካ ውስጥ መግባቱ ለትዝብት መዳረጉ አይቀሬ ነው፡፡ የሆነ ሆኖ ከጥቂት ጊዜያት በኋላም ይኽን ቁጭታቸውን ወደ ተደራጀ የፖለቲካ ትግል በማሸጋገር የስልጤ ህዝብ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ (ስሕዴፓ) የተሰኘ የተቃዋሚ ድርጅት መሰረቱ፡ ፡ በፓርቲያቸው አስተባባሪነትም የተቃውሞ ሰልፍ እስከ ማድርግ ደረሱ፡፡ 
ምንአልባትም የዛሬው ድርጅታቸው ኢህአዴግ አርቆ አሳቢነት የፈጠረው ይሁን ወይም ሌላ፣ ድንገት የሬድዋንን ፓርቲ የሚቃወም አዲስ ፓርቲ ብቅ አለ፣ በአሁኑ ወቅት የመከላከያ ሚኒስትር በሆኑት ሲራጅ ፈርጌሳ አማካኝነት ይመራ የነበረው ይህ ፓርቲ የስልጤ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ድርጅት (ስሕዴድ) ይሰኛል፡፡ … እሾን በእሾህ፣ ፓርቲን በፓርቲ፡፡ እናም የሬድዋን ትግል ከኢህአዴግ ጋር ብቻ መሆኑ ቀርቶ ከሌላኛው የስልጤ ህዝብ ድርጅት ጋርም ሆነ፡፡ በሁለቱ ድርጅቶች መካከልም የከረረ የውክልና ፉክክር ተፈጠረ፡ ፡ በሽግግር መንግስቱ ዘመን ‹‹የኦሮሞን ህዝብ በትክክል የምወክለው እኔ ነኝ›› በሚል በኦነግ እና በኦህዴድ መካከል የነበረው ፉክክር አይነት ወራቤ ላይም ተደገመ፡፡ ቃላቶችን እያሰካኩ ያለማቋረጥ የመናገር ተሰጥኦ ያላቸው ሬድዋንም በአገኙት አጋጣሚ በሲራጅ ፈርጌሳ የሚመራውን ስሕዴድ ‹‹የኢህአዴግ ተላላኪ፣ ተለጣፊ፣ አሻንጉሊት…›› እያሉ ይተቹት እንደነበር የትላንት ትውስታ ነው፡፡ ትውስታችንንም በማስረጃ ለማስደገፍ ያህል ሬድዋን የተቃዋሚ ፓርቲ ሊቀመንበር በነበሩበት ዘመን በ1993 ዓ.ም. ታህሳስ ወር ከታተመው ከጎህ መጽሔት ጋር ከአደረጉት ቃለ መጠይቅ ጥቂቱን እንቀንጭብ፡፡ መጽሔቱም የሳቸውን ድርጅት የማይደግፉ የስልጤ ተወላጆች መኖራቸውን ጠቅሶ ይኼ ከምን የመነጨ እንደሆነ እንዲያብራሩለት ጠየቃቸው፡፡ ሬድዋንም ሲመልሱ እንዲህ አሉ፡- ‹‹…የስልጤን ብሔረሰብ በተለያየ ስያሜ ፈርጀው የተንቀሳቀሱት የብሔረሰቡ ተወላጆች የኋላ ኋላ እውነቱን ቢረዱም ጥቅም ፍለጋ በዚያው ሰክረው ቀሩ እንጂ የተፈጠረው ምስቅልቅል በመጀመሪያ የራሱ የሆኑ መነሻዎች አሉት፡፡›› ሬድዋን ወደ ኢህአዴግ ያዘነበሉትን የስልጤ ተወላጆችን ነው ‹‹ጥቅም ፍለጋ በዚያው ሰክረው ቀሩ›› ሲሉ የወነጅሉት፡፡ በዛ በደጉ ዘመን፡፡ በእርግጥ ዛሬ ሬድዋን እንዲህ ሊሉ አይችሉ፡፡ 
በብራሃን ፍጥነት ራሳቸውም ከዋነኞቹ ኢህአዴጎች አንዱ ሆነዋልና፡፡ ሆኖም ሬድዋን ከኢህአዴግ ተቃዋሚነት ወደ ኢህአዴግ አመራርነት የተሸጋገሩበት ምክንያት ‹‹ጥቅም ፍለጋ በዚያው ሰክረው ቀሩ›› ሲሉ የወነጀሏቸውን ሰዎች ፈለግ ተከትለው ይሁን ወይም የግንባሩ ፖለቲካ አዋጭነት ገብቷቸው ከሳቸው ሌላ የሚያውቅ የለም፡፡
ምንጭ. ባባአ አየዱ

Thursday, August 7, 2014

ኢህአዴግ ከላይ እስከታች የአመራር ችግር ገጠመው:: ኢህአዴግ ፈተና ውስጥ ነው ::

በስጋት በተቀመጡት ክልሎች አሁንም አፋጣኝ ስራ ካልተሰራ ኪሳራ ሊያመጡ ይችላሉ::
የአማራ ክልል አመራሮች ከግንቦት7 የኦህዴድ ደግሞ ከኦነግ ጋር እያበሩ ነው ሲል አቶ አዲሱ ለገሰ ያዘጋጁትና ለጠ/ሚ አማካሪዎች የተላከው ሰነድ አመለከተ በሰነዱ ላይ ኢህአዴግ የአመራር ችግር እንዳጋጠመው፣ የትራንስፎርሜሽኑ እቅድ አለመሳካቱእንዲሁም በጋምቤላ ተማኝ መሪ መጥፋቱ ተዝርዝሯል በሃምሌ ወር መጨረሻ የተዘጋጀው ሰነድ ግልባጭ ለጠ/ሚኒስትሩ አማካሪዎች ለአቶ በረከት ስምኦን፣ ለአቶ ደስታውና ለአቶ ኩማ ደመቅሳ ተደርጓል።

Saturday, August 2, 2014

የሴት ልጅ ግርዛትን የመቀነስ ፈተና

ባለፈው ሳምንት በኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ከተላለፉት ዜናዎች ቀልቤን የሳበው በእንግሊዝ ሎንዶን እየተላለፈ ያለው ስብሰባ (Girls Summit 2014) ነው፡፡ በዜናው እንደተገለጸው የሴት ልጅ ግርዛት እንደዲቆም ያለመው ይህ ስብሰባ
የተወሰኑ አገሮች መሪዎችን፣ መንግሥታዊና የግል ድርጅት ተወካዮችን፣ የአገር ሽማግሌዎችንና ታዋቂ ሰዎችን ያሳተፈ ነው፡፡ እንደ ኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ዘገባ በሴት ልጅ ግርዛት ስፋት በአንደኝነት ከተፈረጁት ውስጥ ሶማሊያ (98%)፣ ጊኒ (97%) ሲገኙበት በሁለተኛ ደረጃ እንደ ጂቡቲ (93%)፣ ግብፅ (91%) ይገኙበታል፡፡ ዘገባው በሦስተኛ ደረጃ ያስቀመጣቸው ኤርትራ (83%) እንዲሁም ሱዳን (88%) አገሮችን ነው፡፡ የኢትዮጵያን በተመለከተ ዘገባው ስፋቱ ምን ያህል እንደሆነ ሳይገልጽ በመቀነስ ደረጃ ለውጥ ካመጡ አገሮች መካከል እነደሆነች ገለጸ፡፡ ለራስ ሲቆርሱ አያሳንሱ ካልሆነ በቀር አገራችን የሴት ልጅ ግርዛት ከተንሰራፋባቸው አገሮች መካከል የተመደበች ሲሆን ስፋቱም 74% እንደሆነ በዚሁ ስብሰባ የወጣው የዩኒሴፍ ሪፖርት አሳይቷል፡፡ ይህ አሃዝ አገራችን የሴት ልጅ ግርዛትን በመቀነስ ረገድ አጠንክራ እንድትሠራ ከሚያደርግ በቀር በምንም መስፈርት ሊያኩራራት ወይም በጣም እንደሠራች በኩራት ልትናገርበት የምትችልበት አይደለም፡፡